በደብረ ማርቆስ ማረሚያ ቤት በደረሰ ቃጠሎ በእስር ላይ የሚገኙ 5 ሰዎች ህይወታቸው ሲያልፍ በርካቶች መቁሰላቸው ተገለፀ፡፡ በተለይ ከስፍራው ምንጮቸችን እንደገለፁት ከሆነ ቃጠሎው የተከሰተው ታህሣሥ 12 ቀን 2005ዓ.ም. ከሌሊቱ 5 ሰዓት እንደሆነ እና እስረኞቹ ላይ ጉዳት ሊደርስ የቻለው በእስር ላይ የሚገኙ ሰዎች ያሉት ክፍል ሲቃጠል በላያቸው ላይ ተዘግቶ የነበረውን በር የሚከፍትላቸው አጥተው እንደነበር አስታውሰዋል፡፡
አዲስ ሚዲያም የቃጠሎውን መንስኤ እና ቃጠሎው ባጠቃላይ ያደረሰውን ጉዳት በተመለከተ የደብረማርቆስ ማረሚያ ቤት አስተዳደርና የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በጉዳዩ ዙሪያ ምላሽ እንዲሰጡን ተደጋጋሚ ጥረት ቢደርግም አልተሳካም፡፡