የአፋር ክልላዊ መንግስት 3 ባለስልጣናት ተሰናበቱ

 

በአፋር ክልላዊ መንግስት ገዥው ፓርቲ አብዴፓ ባካሄደው ጉባዔ የክክሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳደርና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ የሆኑት አቶ አወል ውቲካ እና የአብዴፓ ጽህፈት ቤት ኃላፊ  አቶ መሐመድ ቡልቡል የተሰጣቸውን ኃላፊነት በአግባቡ አልተወጡም  በሚል ሙሉ በሙሉ ከስልጣናቸው ሲነሱ የክልሉ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ስራ አስፈፃሚ አቶ መሐመድ ያዮ ከኃላፊነታቸው ዝቅ መደረጋቸው ታውቋል፡፡ በጉባዔው የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ እስማኤል አሊሴሮ ከክልሉ ህዝብ ጥቅም ይልቅ ለኢህአዴግ ስልጣን ጥቅም ብቻ ይሰራሉ በሚል እየተወቀሱ ውስጥ ውስጡን ከስልጣናቸው እንዲነሱ ቢፈለግም በኢህአዴግ ባለስልጣናት ፍላጎት ሳይወርዱ መቅረታቸውን የአዲስ ሚዲያ ምንጮቻችን ከስፍራው ጠቁመዋል፡፡

በተያያዘ ዜና በአፍር ክልል ዞን ሶስት  በሚገኙ ገዋኔ፣ አሚባራ እና ጉሩመዳች ወረዳ ከሚገኙ አርብቶ አደሮች በፌደራል ፖሊስ  ለከብቶቻቸው ጥበቃ የሚገለገሉበት የጦር መሳሪያ በፌደራል ፖሊስ ተነጥቆ ሲወሰድ የአጎራባች የሶማሌ ክልል ወረዳ ነዋሪዎችም በተመሳሳይ ተነጥቆ ከፍተኛ ቁጣን በመቀስቀሱ ወዲያው ሲመለስላቸው የአፋሮች ግን ሳይመለስ በመቅረቱ ማንነታቸው ባልታወቁ ዘራፊዎች 80 ፍየሎችና 17 የቀንድ ከብቶች እንደተሰረቁባቸው ምንጮቻችን በተለይ ለአዲስ ሚዲያ ገልፀዋል፡፡ የክልሉ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ባልደረባ የሆኑት አቶ መሐመድ ያዮ የተደረገው ሹም ሽር አስመልክቶ፣  የአርብቶ አደሮቹ መሳሪያ መነጠቅ ላይ እና ተፈፀመባቸው ስለተባለው ዝርፊያ መልስ ለመስጠት ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: