ህዝበ ሙስሊሙ “313 ሚሊዮን ብር ለልማት” በሚል ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ አደረገ

ብስራት ወ/ሚካኤል

ህዝበ ሙስሊሙ አርብ ሚያዝያ 18 ቀን 2005 ዓ.ም በአንዋር መስጂድ “313 ሚሊዮን ብር ለልማት” የሚል
መፈክር እያስተጋባ ተቃውሞውን አሰማ፡፡ ለጁምዓ ስግደት የወጣው የሙስሊሙ ህብረተሰብ ከስግደት በኋላ “313
ሚሊዮን ብር ለልማት” የሚል መፈክር አሰምቶ በሰላም ወደ የቤቱ ተበትኗል፡፡

የዕለቱ መፈክር ምን ማለት ነው? ለምን አስፈለገ? ምን መልዕክት ለማስተላለፍ ተፈልጎ ነው በማለት በሥፍራው
ለነበሩ አንድ የሙስሊየም ሃይማኖት ተከታይ ፍኖተ ነፃነት ጥያቄ አቅርቦ   “መንግስት አህባሽ የተባለ ባዕድ
አስተምሮ አስመጥቶ ለማስፋት 313 ሚሊዮን ብር በጀት ለመጅሊሱ መመደቡን የሚያሳይ ሰነድ አግኝተናል፡፡ ይህ
በጣም ያሳዝናል፡፡ መንግስት በሃይማኖት ውስጥ ጣልቃ አልገባም እያለ ይክዳል፡፡ በተግባር ግን በጀት መድቦ
ሙስሊሙን ህብረተሰብ ለማተራመስ ይሠራል፡፡ ወታደርና ደህንነት አሰልፎም የእምነት ነጻነታችንን አፍኗል፡፡
በነጻነት እንዳናመልክ የእምነት ሥፍራችንን ይዳፈራል፡፡ ስለዚህ ሃይማኖታችንን ለመበከል ሙስሊሙን ለመከፋፈል
የመደበውን በጀት ለልማት እንዲያውለው ለማሳሰብ ነው” በማለት ምላሽ ሰጥተዋል፡፡  አያይዘውም “ለልማት እያለ
ህዝብን ከማስጨነቅ በእጁ ያለውን ገንዘብ በመጀመሪያ ለልማት እንዲያውለው ለመጠየቅ መጥተነል” ሲሉ የተቃውሞ
ሰልፉን አላማ አስረድተዋል፡፡

ከሀሙስ ዕለት ጀምሮ በተለያዩ መስጂዶች ሁለት ገጽ ያለው በራሪ ወረቀት የተበተነ ሲሆን፤ “68ኛ የተቃውሞ
ሳምንት ድምጽ፤ ቁጥር 42” የሚለው ይኸው በራሪ ወረቀት ስድስት አብይ ርዕሶችን በመያዝ ይዘረዝራል፡፡ እነሱም
ሰላማዊነታችን ከሌሎች እምነት ተከታይ ወንድሞቻችን ድጋፍ አስገኝቶልናል፣ ሰላማዊነታችን ዓለም አቀፍ ዲፖሎማሲያዊ
ድጋፍ አስገኝቶልናል፣ ሰላማዊነታችን ትግላችን ዕድሜና ክብር እንዲጎናፀፍ አስችሎናል፣ ሠላማዊ ትግል ለእርማት
ሁል ጊዜ ክፍት ነው፣ ሠላማዊነታችን ከአስከፊ እርምጃዎች እንድንጠበቅ ሰበብ ሆኖናል የሚልና ሠላማዊ ትግል
ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ማሰለፍ ይችላል የሚሉት ነጥቦች ናቸው፡፡
ህዝበ ሙስሊሙ አርብ ሚያዝያ 18 ቀን 2005 ዓ.ም በአንዋር መስጂድ “313 ሚሊዮን ብር ለልማት” የሚል
መፈክር እያስተጋባ ተቃውሞውን አሰማ፡፡ ለጁምዓ ስግደት የወጣው የሙስሊሙ ህብረተሰብ ከስግደት በኋላ “313
ሚሊዮን ብር ለልማት” የሚል መፈክር አሰምቶ በሰላም ወደ የቤቱ ተበትኗል፡፡

የዕለቱ መፈክር ምን ማለት ነው? ለምን አስፈለገ? ምን መልዕክት ለማስተላለፍ ተፈልጎ ነው በማለት በሥፍራው
ለነበሩ አንድ የሙስሊየም ሃይማኖት ተከታይ ፍኖተ ነፃነት ጥያቄ አቅርቦ   “መንግስት አህባሽ የተባለ ባዕድ
አስተምሮ አስመጥቶ ለማስፋት 313 ሚሊዮን ብር በጀት ለመጅሊሱ መመደቡን የሚያሳይ ሰነድ አግኝተናል፡፡ ይህ
በጣም ያሳዝናል፡፡ መንግስት በሃይማኖት ውስጥ ጣልቃ አልገባም እያለ ይክዳል፡፡ በተግባር ግን በጀት መድቦ
ሙስሊሙን ህብረተሰብ ለማተራመስ ይሠራል፡፡ ወታደርና ደህንነት አሰልፎም የእምነት ነጻነታችንን አፍኗል፡፡
በነጻነት እንዳናመልክ የእምነት ሥፍራችንን ይዳፈራል፡፡ ስለዚህ ሃይማኖታችንን ለመበከል ሙስሊሙን ለመከፋፈል
የመደበውን በጀት ለልማት እንዲያውለው ለማሳሰብ ነው” በማለት ምላሽ ሰጥተዋል፡፡  አያይዘውም “ለልማት እያለ
ህዝብን ከማስጨነቅ በእጁ ያለውን ገንዘብ በመጀመሪያ ለልማት እንዲያውለው ለመጠየቅ መጥተነል” ሲሉ የተቃውሞ
ሰልፉን አላማ አስረድተዋል፡፡

ከሀሙስ ዕለት ጀምሮ በተለያዩ መስጂዶች ሁለት ገጽ ያለው በራሪ ወረቀት የተበተነ ሲሆን፤ “68ኛ የተቃውሞ
ሳምንት ድምጽ፤ ቁጥር 42” የሚለው ይኸው በራሪ ወረቀት ስድስት አብይ ርዕሶችን በመያዝ ይዘረዝራል፡፡ እነሱም
ሰላማዊነታችን ከሌሎች እምነት ተከታይ ወንድሞቻችን ድጋፍ አስገኝቶልናል፣ ሰላማዊነታችን ዓለም አቀፍ ዲፖሎማሲያዊ
ድጋፍ አስገኝቶልናል፣ ሰላማዊነታችን ትግላችን ዕድሜና ክብር እንዲጎናፀፍ አስችሎናል፣ ሠላማዊ ትግል ለእርማት
ሁል ጊዜ ክፍት ነው፣ ሠላማዊነታችን ከአስከፊ እርምጃዎች እንድንጠበቅ ሰበብ ሆኖናል የሚልና ሠላማዊ ትግል
ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ማሰለፍ ይችላል የሚሉት ነጥቦች ናቸው፡፡

ምንጭ ፡- ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: