አንዱዓለም አራጌ በእስር ቤት…

Aneduየአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ከፍተኛ አመራር አቶ አንዱዓለም አራጌ የመጀመሪያ ልጁን የሩህ አንዱዓለምን 5ኛ ዓመት የልደት በዓል እሁድ ግንቦት 11 ቀን 2005ዓ.ም. አከበሩ፡፡ አቶ አንዱዓለም አራጌ የልጃቸውን የልደት በዓል እቤታቸው ማክበር ባለመታደላቸው እሁድ ከቀኑ 4፡00 ሰዓት ለባለቤታቸው ሳያሳውቁ ለመጠየቅ ሲሄዱ በድንገት ለማስደሰት ሲሉ ተዘጋጅተው በመጠበቃቸው በሰዓቱ ባለቤታቸው ዶ/ር ሰላም አስቻለው፣ልጃቸው ሩህ አንዱዓለም፣እህታቸው ወ/ት አበሩ አራጌ በተገኙበት በመጠየቂያ ጠባብ ክፍል በጋራ የልጃቸውን ልደት አክብረዋል፡፡

ይህ ልጃቸው ያኔ ረቡዕ መስከረም 3 ቀን 2003ዓ.ም. ለመጀመሪያ ጊዜ ትምህርት ቤት ልኮት ማታ ሲመጣ ውሎውን ለማዳመጥ በናፍቆት እየጠበቀና ይህንንም ለባልደረቦቹ ለአንድነት ፓርቲ አመራሮችና ሰራተኞች የነገረ ቢሆንም በዕለቱ የልጁን ውሎ እንደናፈቀ ከቀኑ 9፡20 ሰዓት ላይ በፖሊሶች ከሚሰራበት ከፓርቲው ዋና ፅህፈት ቤት አቅራቢያ ካለ ካፍቴሪያ ከአንድ የፓርቲው ወጣት አመራር ጋር በመሆን ሻይ ቡና ብለው ሲወጡ ተይዘው መታሰራቸው ይታወቃል፡፡

በዕለቱ የዛሚ ሬዲዮ ባለቤት ሚሚ ስብሐቱ የእነ አንዱዓለም ፓርቲ ልሳን የሆነውን ፍኖተ ነፃት ጋዜጣን ዋቢ አድርጋ በመጥቀስ ብጥብጥ እየቀሰቀሱ ነው፤ ዝም ሊባሉ አይገባም ብላ በተለመደቀው በቀትር የጋዜጠኞች ክብ ጠረጴዛ ዙሪያ በሚል የሬዲዮ መርሃ ግብር አቅርባ የነበረ ሲሆን አንዱዓለምም ይህንን ከሌሎች ባልደረቦቹ ጋር አዳምጦ ጨርሶ ከወጣ በኋላ መያዛቸው አዘነጋም፡፡ በአሁን ወቅትም ወጣቱ ፖለቲከኛ አቶ አንዱዓለም አራጌ የእድሜ ልክ ፅኑ እስራት ተፈርዶባቸው በቃሊቲ እስር ቤት እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡

ምንጭ፡- ኢቦኒ መፅሔት(ግንቦት 2005ዓ.ም.)

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: