በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው የመጀመሪያው ማጣሪያ ጨዋታ በናይጄሪያ አሸናፊነት ተጠናቀቀ

 

bbbየኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን ለብራዚሉ ዓለም ዋንጫ 2014 ማጣሪያ በአዲስ አበባ ስታዲየም ዛሬ ጥቅምት 3 ቀን 2006 ዓ.ም. ከናይጄሪያ አቻው ጋር ባደረገው ጨዋታ 2 ለ 1 ተሸነፈ፡፡ በውጤቱም ኢትዮጵያ 1፡ 2 ናይጄሪያ በመሆን ተጠናቀቋል፡፡ በጨዋታውም የኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ከፍተኛ ብልጭ የበላይነቱን ቢያረጋግጥም፤የኢትዮጵያ የፊት አጥቂ ሳላዲን ሰይድ ያገባት ጎል በዳኛው ተሽራለች፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን የበረኛው ክልል አካባቢ በተፈጠረ የቴክኒክ ችግር ባለቀ ሰዓት ናይጄሪያ ልታሸንፍ ችላለች፡፡

ሁለቱም ቡድኖች ጎሉን ያስቆጠሩት በሁለተኛ አጋማሽ ሰዓት ሲሆን ለኢትዮጵያ በ56ኛው ደቂቃ የመሪነት ጎሉን በግራ አቅጣጫ ያስቆጠረው በኃይሉ አሰፋ (ቱሳ) ነው፡፡ ናይጄሪያ ደግሞ አንዱን በጨዋታ ስታገባ ሁለተኛውን ጎል ግን በተሰጣት ፍፁም ቅጣት ምት ነበር፡፡ በተለይ የአዲስ አበባ ስታዲየም በተመልካቾች የብሔራዊ ቡድኑን መለያ በመልበስ እጅግ አሸብርቀው ለሜዳው ደምቀት ሰጥተውታል፡፡ ቀጣዩ የደርሶ መልስ በናይጄሪያ በሚደረገው ጨዋታ ለዓለም ዋንጫ የመጨረሻው ውጤት ይታወቃል፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: