የመጅሊስ እና የዑለማዎች ምክር ቤት የይፍረሱ ክስ ለሰበር ሰሚ ችሎት እንደሚቀርብ ተገለፀ

የኢትዮጵያ እስልምና እና የዑለማዎች ምክር ቤት ይፍረሱ በሚል የቀረበው አቤቱታ ውድቅ ከተደረገ በኋላ ፤ በድጋሚ ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት እንደሚቀርብ ኢትዮ ምህዳር ጋዜጣ ጥቅምት 6 ቀን 2006 ዓ.ም. ባወጣው እትሙ አስነብቧል፡፡

muslimsየታሰሩት የኢትዮጵያ ሙስሊም ችግሮች መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ጠበቃ ተማም አባ ቡልጉ እንደተናገሩት፤ የተጀመረው ክስ ለመስከረም 27 ቀን 2006 ዓ.ም. ድጋሚ ያስቀርባል አያስቀርብም የሚለውን ለማየት እንደነበር ተናግረው ፤ ጉዳዩ ተብራርቶ በመቅረቡ ለማክሰኞ ጥቅምት 5 ቀን 2006 ዓ.ም. ሰበር ሰሚ ችሎት እንደሚሰየም ጋዜጣው ቢዘግብም የማክሰኞ ችሎት ውሎውን በመለከተ ግን ያለው ነገር የለም፡፡

እንደጋዜጣው ዘገባ ከሆነ ፤ ዑለማዎች ምክር ቤት በራሱ በእስልምና ጠቅላይ ጉባዔዎች ስር ያለ በመሆኑ እና የነዚህ የበላይ ደግሞ መጅሊሱ በመሆኑ ዑለማዎች ምክር ቤት የማስመረጥ መብት የለውም የሚለው የክሱ አንዱ ጭብጥ መሆኑን ጠበቃ ተማም መናገራቸው ተዘግቧል፡፡ እንደጠበቃ ተማም ገለፃ፤ ዑለማዎች ምክር ቤት ምርጫ ያካሄደው የራሱ የሆነ ህጋዊ ሰውነት ሳይኖረው ነው፡፡ ምርጫውን የማካሄድ ስልጣን የዑለማዎች ምክር ቤት ሊሆን አይችልም፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: