የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች የመንግስትን ማጭበርበር አጋለጡ

ኢትዮጵያውያን ጋዜጠኞች ዛሬ ጥቅምት 30 ቀን 2006 ዓ.ም. ከCPJ ፣ ከዶሃ ዓለም አቀፉ የሚዲያ ነፃነት ማዕከል እና ከሌሎች ዓለም አቀፍ የሚዲያ ተቋማት ተወካዮች ጋር በአዲስ አበባ ኢሊሊ ኢንተርናሽናል ሆቴል ተገናኝተው ተወያዩ፡፡ ጋዜጠኞቹ ለ3፡30 ሰዓት ያህል ስለኢትዮጵያ ሚዲያ አፈና፣ ስለጋዜጠኛች መከራ፣ እስርና ስቃይ እንዲሁም ስደት ከነነባራዊው ሁኔታ በዝርዝር ከነ ምክንያቱ ሰፊ ምክክር ተደርጓል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ትናንት ጥቅምት 29 ቀን 2006ዓ.ም በአፍሪካ የኢኮኖሚክ ኮሚሽን የተደረገው የአፍሪካ ሚዲያ ፎረም ላይ ነፃ ጋዜጠኞች እንዳልተጋበዙ እና የመንግስት ደጋፊዎች እንዲሳተፉ መደረጉን እንዲሁም ከነፃ ሚዲያ ከ3 ያልበለጡ በእንግሊዘኛ የሚዘጋጅ ሚዲያ አዘጋጆች በሌላ አካል እንዲሳተፉ መደረጉን፣ መንግስት ሚዲያውን ከማፈኑ በተጨማሪ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ፣ ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ፣ ጋዜጠኛ ዩሱፍ ጌታቸውን ጨምሮ 6 ጋዜጠኖች ከጋዜጠኝነት ስራ ጋር በተያያዘ መታሰራቸው እና በተለያየ ጊዜም የተለያዩ ጋዜጠኞች እየታሰሩ እንደሚፈቱ ተጠቁሟል፡፡

በዚህም ዙሪያ በአፍሪካ ሚዲያ ፎረም ላይ ስለተጋበዙ ስለኢትዮጵያ ጋዜጠኞች እና ሚዲያ አፈና የተሳሳተ ዘገባ እንዳያቀርቡ እውነታውን ከ15 ያላነሱ ጋዜጠኞች አብራርተዋል፡፡ በዚህም ጋዜጠኖቹ የመንግስትን ማጭበርበር በማጋለጣቸው፤ ተወካዮቹ እውነታውን ለዓለሙ ማኀበረሰብ እነምደሚያቀርቡ እና ይህንንም በይበልጥ ለለጋስ ሀገሮች እንደሚያሳውቁ በማረጋገጥ ውይይቱ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: