በአዲስ አበባ የሚገኘው የአፍሪካ ትልቁ የንግድ ማዕከል መርካቶ ዛሬ ህዳር 25 ቀን 2006 ዓ.ም. ከቀኑ 8፡00 ሰዓት በኋላ በመርካቶ ልዩ ቦታው ከምዕራብ ሆቴል ወደ በርበሬ በረንዳ በሚወስደው መንገድ ሐረር ሜትሮ ሆቴል ዓለም ሽንሽን እና ጌጣጌጥ በሚሸጡባቸው ሱቆች እና በተለምዶ ጆንያ ተራ እየተባለ በሚጠራው ቦታ በተነሳ የድንገተኛ ችሳት ቃጠሎ እስካሁን ግምቱ ያልታወቀ ንብረት አውድሟል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር እሳት እና ድንገተኛ አደጋ መከላከያ ድርጅት እሳቱን ለማጥፋት በቶሎ ባለመድረሱ ብዙ መትረፍ የሚገባቸው ንብረቶች ሊወድሙ መቻላቸው የታወቀ ሲሆን፤ ድርጅቱ በበኩሉ ወደ መርካቶ መሄጃ መንገዶች በመቆፋፈራቸው ለመዘግየቱ እንደምክንያት ተጠቅሷል፡፡ በአካባቢው ያሉ እማኞች በበኩላቸው ድርጅተሩ በከተማው መቼም ቢሆን በአፋጣን ደርሶ ውድመትን አድኖ አያውቅም፤ ብዙ ንብረት ማትረፍ ሲቻል ብዙ ጊዜ ሆን ብሎ በሚመስል መልኩ ይዘገያል የሚል ትችትን አቅርበዋል፡፡