የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ፍርድ በአየር ለሌላ ጊዜ ተቀጠረ

የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች የመጨረሻ ፍረድ ብይን ዛሬ ህዳር 23 ቀን 2006 ዓ.ም. ይሰጣል ተብሎ ቢጠበቅም ያለምንም ችሎት በአየር ላይ ለሌላ ጊዜ መቀጠሩ ታወቀ፡፡ ቀደም ሲል ጉዳዩ ልደታ ከሚገኘው ከፍተኛው ፍርድ ቤት አቃቂ ቃሊቲ በሚገኘው ደራርቱ ቱሉ ትምህርት ቤት አካባቢ በሚገኘው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በዝግ ችሎት እየታየ የነበረ ሲሆን፤ በብዙዎች ግምት የመጨረሻ የብይን ፍርዱ ልደታ በሚገኘው ፍርድ ቤት ይሆናል ተብሎ ሲጠበቅ በሁለቱም ፍርድ ቤት ችሎት አለመሰየሙ ታውቋል፡፡

ይሁን እንጂ ጋዜጠኞች፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና ዓለም አቀፍ ዲፕሎማቶች ጉዳዩን እንዳይከታተሉ በዝግ ችሎት ሲያደርግ የቆየው አቃቂ ቃሊቲ የሚገኘው ፍርድ ቤት ዛሬ በመዝገብ ቤት በኩል ለአንዱ ተከላካይ ጠበቃ የመጨረሻ ይሆናል የተባለውን የፍርድ ብይን ለታህሳስ 3 ቀን 2006 ዓ.ም. ያለ ምንም ችሎት በአየር ላይ ቀነ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ ተከላካይ ጠበቆችም ከፍርድ ቤት አሰራር ውጭ ያለምንም ችሎት ቀነቀጠሮ መሰጠቱ እንዳስገረማቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: