መኢአድና አንድነት በባህርዳር ከተማ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ጠሩ

 

Imageዛሬ የካቲት 6 ቀን 2006 ዓ.ም. በአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት መኢአድና አንድነት በጋራ ሰላማዊ ሰልፍ ጠሩ፡፡ ፓርቲዎቹ ሰላማዊ ሰልፉን የጠሩት የፊታችን ካቲት 16 ቀን 2006 ዓ.ም. በባህርዳር ከተማ ሲሆን ፤ ለዚህም ዋነኛው ምክንያት ባለፈው የብአዴን/ኢህአዴግ ምክትል ሊቀመንበርና ዋና ፀሐፊ የሆኑት አቶ አለምነው መኮንን አማራን ህዝብ በማጥላላት ስድበ አዘል ንግግር ማድረጋቸውን በመቃወም ነው፡፡ 

ፓርቲዎቹ በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳስታወቁት ከሆነ አቶ አለምነው መኮንን የሚባሉት የብአዴን/ኢህአዴግ አመራር ህዝብን በመዝለፍና በማዋረድ በይፋ ህግ የጣሱ ቢሆኑም እስካሁን ፓርቲያቸውም ሆነ እራሳቸው ህዝቡን ይቅርታ አልጠየቁም፡፡ ይህም የሚያሳየው ለህዝብ ያላቸውን ንቀት የሚያሳይ በመሆኑ ለፍርድ ቀርበው ተገቢውን ቅጣት ሊያገኙ ይገባል፤ ከዚህ ጋር ተያይዞ የፊታችን የካቲት 16 ቀን 2006 ዓ.ም. ከተጠራው የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ በተጨማሪ በሌሎችም የሀገራችን ከተሞች የተቃውሞ ሰልፉ ይቀጥላል፣ ህዝብን እየናቁ ህዝብን ማስተዳደርም ሆነ መምራት አይቻልም ሲሉ አስታውቀዋል፡፡

በመግለጫው እንደተገለፀው የሰልፍ ማሳወቂያው ደብዳቤ በሁለቱም ፓርቲዎች ለሚመለከተው የባህርዳር ከተማ መስተዳደር ገቢ መደረጉምን ገልፀዋል፡፡ የባህርዳርና አካባቢው ህዝብም በነቂስ በመውጣት በተቃውሞ ሰልፉ ላይ እንዲገኝ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡

 

 

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: