በሐረር የተከሰተው ተደጋጋሚ የእሳት አደጋ ጥያቄ ማስነሳቱን ቀጥሏል

 

በታሪካዊቷ ሐረር ከተማ ባለፈው ካቲት 30 ቀን 2006 ዓ.ም. በሸዋበር የንግድ ሱቆች ላይ በተደጋጋሚ የደርሰው የእሳት አደጋ የከተማው ነዋሪና የአካባቢው የንግድ ማኀበረሰብ ላይ ከፍተኛ ጥርጣሬ በመፍጠሩ ጥያቄ ማስነሳቱ ዛሬም ቀጥሏል፡፡ ሁለት ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ሶስት ጊዜ ሱቆቻቸው የተቃጠለባቸው እና አሁንም ለከፍተኛ ኪሳራ የተዳረጉም እንዳሉ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ የከተማው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ በተደጋጋሚ ስለሚነሳው የእሳት አደጋ ምክንያት አደጋው የደረሰባቸው መንግስት ተገቢውን ጥበቃ አላደረገም በሚል ሰልፍ ከመውጣታቸው ጋር ተያይዞ መንግስት አደጋው ለደረሰባቸው ነጋዴዎች ምን እንዳሰበ በጋዜጠኛ ተጠይቀው፤ ሰልፍ የወጡት የጎዳና ተዳዳሪዎች ናቸው፣እርምጃ እንወስድባቸዋለን ማለታቸው ይበልጥ ቁጣመቀስቀሱን ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ ምንም እንኳ እስካሁን የእሳት አደጋው መንስኤ ተጣርቶ ይፋ ባይሆንም እንደምንጮች ገለፃ ከሆነ ከተፈጠረው እሳት አደጋ ጀርባ የመንግስት እጅ ሳይኖርበት አይቀርም በሚል የህዝብ ግንኙነቷን መልስ ዋቢ በማድረግ ነዋሪዎቹ ጥርጣሬ እንዳላቸው ጠቁመዋል፡፡hara

በከተማው የንግድ ሱቆች ላይ በተደጋጋሚ እየተከሰተ ስላለው የእሳት አደጋ ጋር በተያያዘ የጠየቅናቸው አቶ አብዱላሂ እንዳሉት ከሆነ፤ አደጋውን የክልሉ ባለስልጣናት ሆን ብለው እንዳደረጉትና መሬቱን ለራሳቸው ሰዎች ለመስጠት አስበው ሊሆን እንደሚችል ጥርጣሬ እንዳላቸው ጠቁመዋል፡፡ ለዚህም በምክንያትነት ያነሱት ከአንድ ሺህ ዓመታት በላይ ያስቀጠረችና እና በዓለም ቅርስነት በዩኔስኮ የተመዘገበች ታሪካዊ ከተማ ያውም በንግድ ሱቆች ላይ ተደጋጋሚ የእሳት አደጋ መከሰቱ ከመንግስት ሌላ እጅ ይኖራል ተብሎ አይታሰብም፣ ይህም በከተማው ወደፊት ኢንቨስት ለማድረግ የሚፈልጉ ዜጎችንም ሆነ የውጭ ባለሃብቶች የሚያበራታታ አይደለም ብለዋል፡፡har

በአደጋው እስካሁን በቁጥር ተለይቶ ባይታወቅም እጅግብዙ ንብረቶች መውደማቸውም ተጠቁሟል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሙራድ አብዱላሂ በአደጋው ንብረቶቻቸው ለወደመባቸው ነጋዴዎች መንግስት በጀት መመደቡን ማስታወቃቸው የተነገረ ሲሆን፤ አንዳንድ ነጋዴዎች ግን ስለተግባራዊነት ጥርጣሬ እንዳላቸው አልሸሸጉም፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: