ዞን 9 ብሎገሮች ሌላ ቀጠሮ ተጠየቀባቸው፤ የፖሊስየ28 ተጨማሪ ቀናት ጥያቄ ውድቅ ተደርጓል

የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠረጠርኳቸው ያላቸውን 9 ጋዜጠኞች እና ብሎገሮች ሚያዝያ 2006 ዓ.ም.ቢያስርም እስካሁን ምንም ዓይነት ህጋዊ ክስ ሳይመሰርት፤ ዛሬ ሰኔ 22 ቀን 2006ዓ.ም. በድጋሚ ተለዋጭ ቀነ ቀጠሮ ጠይቋል፡፡ ፖሊስ ለፌደራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ ወንጀል ችሎት ዛሬ ቀጠሮ የነበራቸውን እና በማዕከላዊ ያሰራቸውን የዞን 9 ብሎገሮች መካከል በፍቃዱ ኃይሉ፣ ማህሌት ፋንታሁን እና አቤል ዋበላን ይዞ ቢቀርብም፤ እንደተለመደው የቴክኒክ ምርመራዬን አልጨረስኩም፣ ከተሰከሳሾች የተገኙ መረጃዎች ተተርጉመው አላለቁም፣…የሚሉ ምክንያቶችን በመጥቀስ ተጨማሪ የ28 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እንዲሰጠው መጠየቁ ተሰምቷል፡፡

hgtፍርድ ቤቱ እስካሁን የተሰጠው ጊዜ በቂ ነው በማለት የተጠየቀውን የ28 ቀናት ውድቅ ቢያደርግም፤ ፖሊስ ምርመራው አጠናቆ እንዲቀርብ የ14 ቀናት ጊዜ በመስጠት ለሐምሌ 6 ቀን 2006ዓ.ም.ተለዋጭ ቀነ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ይሁን እንጂ ዕለቱ እሁድ ቀን የሚውል በመሆኑ እና መዝገቡ ከእንግዲህ በተዘዋዋሪ ተረኛ ዳኛ ሳይሆን በመደበኛ ችሎት መታየት ስላለበት ለሰኞ ሐምሌ 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ከቀኑ 8፡00ሰዓት ተለዋጭ ቀነ ቀጠሮ መሰጠቱን ከተከላካይ ጠበቃቸው አቶ አምሃ መኮንን መረዳት ተችሏል፡፡ ጉዳዩ ሲታይ የነበረው ከሌሎች ቀናት በተለየ ዛሬ ቤተሰብም በችሎቱ ላይ እንዳይታደም ተከልክሏል፡፡

በፍርድ ቤቱ ግቢ በርካታ የእስረኞቹ ቤተሰቦች፣ ወዳጅ ዘመዶች፣ ዓለም አቀፍ ዲፕሎማቶች እና ጋዜጠኞች ቢገኙም አንዳቸውም ችሎቱን እንዲከታተሉ አልተፈቀደም ነበር፡፡ ፖሊስ ያሰራቸውን ተጠርጣሪዎች ይዞ ወደ ችሎት ሲገባ በፍርድ ቤቱ ግቢ ችሎቱን ለመታደም ከመጡት መካከል ዮናታን ተስፋዬ እና ምኞት የሚባሉ ወጣቶችን በሞባይል ፎቶ ለማንሳት ሞክራችኋል በሚል ወደ ማዕከላዊ ይዟቸው የሄዱ ሲሆን፤ ከሰዓታት በኋላ መለቀቃቸው ታውቋል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ እስካሁን ምንም ክስ ሳይመሰረትባቸው በእስር ላይ የሚገኙት ቀሪዎቹ 6ቱ ጋዜጠኞች እና ብሎገሮች የፊታችን ሐምሌ 5 ቀን 2006 ዓ.ም. ጠዋት ቀነ ቀጠሮ እንዳላቸው ይታወቃል፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: