የአዲስ ጉዳይ መፅሔት ጋዜጠኞች ተሰደዱ

በመንግስት በደረሰባቸው ጫና እና ክስ ምክንያት የ”አዲስ ጉዳይ” መፅሔት ማኔጂንግ ዳይሬክተር እንዳልካቸው ተስፋዬ፣ ምክትል ዋና አዘጋጅ ኢብራሂም ሻፊ፣ ከፍተኛ አዘጋጅ እንዳለ ተሺ እና አዘጋጅ እና የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ (ኢጋመ) ገንዘብ ያዥ ሀብታሙ ስዩም ሀገር ጥለው ተሰደዱ፡፡ ጋዜጠኞቹ የተሰደዱት፤ የፍትህ  ሚኒስቴር አቃቤ ህግ በኢቴቪ አዲስ ጉዳይ መፅሔትን ጨምሮ 5 መፅሔቶች እና አንድ ጋዜጣ ላይ ክስ መመስረቱ ይፋ መደረጉን ተከትሎ ቢሆንም፤ ቀደም ሲል በመንግስት ደህንነትና ፀጥታ ኃይሎች ተደጋጋሚ ጫና ይደርስባቸው እንደነበርም ተጠቁሟል፡፡

addከአዲስ ጉዳይ መፅሔት ከፍተኛ አዘጋጅ አስማማው ኃይለጊዮርጊስ እና የፎቶ ጋዜጠኛ አዚዛ መሐመድ በቅርቡ መታሰራቸውና ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ እንደሚገኝ  ይታወቃል፡፡ የተሰደዱ ጋዜጠኞች ቁጥርም እየጨመረ ሲሆን፤ በቅርቡ የኢትዮጵ ጋዜጠኞች መድረክ ፕሬዘዳነት ጋዜጠኛ በትረ ያዕቆብ እና የህዝብ ግንኙነቱ ዘሪሁን ሙሉጌታን ጨምሮ እስካሁን የተሰደዱ ጋዜጠኞች ቁጥር ከ15 በላይ መሆኑን መረጃዎች አመልክተዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ሌሎችም ጋዜጠኞች ከፍተኛ ጫና ላይ መሆናቸው ታውቋል፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: