ኢትዮጵያውያን በቤልጂየም ብራሰልስ የአውሮፓ ህብረት ዋና ጽህፈት ቤት ፊትለፊት የተቃውሞ ሰልፍ አደረጉ

europeዛሬ አርብ ጥቅምት 29 ቀን 2007 ዓ.ም. በተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን፤ ገዥው ስርኣት በዜጎች ላይ እየፈፀመ ያለውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት በመቃወም የአውሮፓ ህብረት ዋና ፅህፈት በሚገኘው ቤልጂየም ብራሰልስ  ፊት ለፊት የተቃውሞ ሰልፍ አደረጉ፡፡ ሰልፈኞቹ መንግስት በሽብር ስም አስሮ ክስ የመሰረተባቸውን እና የፈረደባቸውን የኢትዮጵያ የህሊናና የፖለቲካ እስረኞችን ፎቶ ግራፎችን በመያዝ፣ በተለያየ የሀገሪቱ አካባቢ በመንግስት የጅምላ ጭፍጨፋ ሰለባ የሆኑ ዜጎችን በማሰብና በሀገሪቱ እየደረሰ ያለውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት በግልፅ በመኮንን፤ የአውሮፓ ህብረት ሀገራትም እንዲህ ዓይነት ድርጊቱ በዜጎቹ ላይ ከሚፈፅም ስርዓት ጋር ትብብር ማድረጋቸው አቁመው ፖሊሲያቸውንና አቋማቸውን እንዲመረምሩ የሚጠይቅ ደብዳቤም ለህብረቱ ፅህፈት መግባቱን በስፍራው የነበሩ ምንጮች አስታውቃል፡፡

ሰልፈኞቹ ተቃውሟቸውን በብራሰልስ የአውሮፓ ህብረት ዋና ፅህፈት ካደረጉ በኋላ በከተማው ወደሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በመሄድ በሀገሪቱ እየተፈፀመ ያለውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ማውገዛቸውን ተሰምቷል፡፡  የተቃውሞ ሰልፉን አስመልክቶ ከአውሮፓ ህብረትም ሆነ ከኢትዮጵያ ኤምባሲ የተገኘውን ዝርዝር ምላሽ በተመለከተ መረጃው እንደደረስን እናቀርባለን፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: