አክሱም የሚገኘው ፅላተ ሙሴ ተሰርቋል መባሉ ፍጹም ሐሰት ነው – የቤተክርስቲያኗ አስተዳዳሪ

ከዛሬ 3 ሺህ ዓመታት በፊት የጠቢቡ ንጉስ ሰሎሞን ልጅ በሆነው ቀዳማዊ ምኒልክ ዘመን ወደ ኢትዮጵያ የመጣው የሙሴ ፅላት መዘረፉን በተለያዩ የማህበራዊ ድረገፆች እና መገናኛ ብዙኃን ተዘግቧል፡፡ ይሁን እንጂ የርዕሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ማርያም ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ እና ማዕከላዊ አክሱም ሀገረ ስብከት ዋና ስራ አስኪያጅ ንብረእድ አባ ገ/ህይወት ገ/ሚካኤል በበኩላቸው የተባለው ጉዳይ ከእውነት የራቀ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

axumለፖሊስም ሆነ ለጠቅላይ ቤተ ክህነት እንዲሁም ለሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስና ለፓትርያርኩ ጽ/ቤት ይህን መሰሉን ሪፖርት አላቀረብንም ያሉት አስተዳዳሪው፤ ወሬው ከየት መጥቶ እንደተወራ አናውቅም ብለዋል፡፡

የአክሱም ጽዮን ማርያም ታቦት በቤተክርስቲያኒቱ ከጥቂት ሰዎች በስተቀር ማንም ሊያየው በማይችለው እና በጥንቃቄ ቦታ እንደሚቀመጥም አስተዳዳሪው ተናግረዋል፡፡ አስተዳዳሪው ጉዳዩንም ለብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በስልክ ደውለው እንደነገሯቸው ተናግረዋል፡፡

ጽላቱ በቤተክርስቲያኒቱ ጠባቂዎች እና በመንግስት የፖሊስ ሃይሎች ከፍተኛ ጥበቃ እየተደረገለት ነው ያሉት አስተዳዳሪው ህዝቡ በቀጣይ የሚከበረውን አክሱም ጽዮን ክብረ በአልን በተረጋጋ መንፈስ እንዲያከብር ጥሪ አቅርበዋል፡፡

 

ምንጭ፡- ድሬ ቲዩብ

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: