ጅማ አንድ እናት እስከነልጃቸው በአሰቃቂ ሁኔታ በፖሊሶች ተገደሉ

ካለፈው አንድ ወር ጀምሮ በአካባቢው የሰፈሩ የፌደራል ፖሊስ አባላት በህዝቡ ላይ የሚወስዱት እርምጃ እየተባባሰ መጥቶ ረቡዕ ሌሊት ለሃሙስ አጥቢያ ፣ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ የፌደራል ፖሊሶች ወደ አንድ ወጣት መኖሪያ ቤት ሰብረው በመግባት እርሱንና እናቱን በአምስት አምስት ጥይኦች በአሰቃቂ ሁኔታ ገድለው ወደ ካምፓቸው አምርተዋል። የከተማው ህዝብ ተቃውሞውን ለማሰማት ሃሙስ ጠዋት ወደ አደባባይ ቢወጣም የጠበቀው የፖሊስ ዱላ ነው።

jimmaየመረጃ ምንጮች እንደገለፁት ከሆነ ወ/ሮ መንበረ የተባሉ የከተማዋ ነዋሪ በሆቴል አገልግሎት ኑሮአቸውን የሚገፉና በአካባቢው ህብረተሰብ ዘንድ የሚከበሩ ልጃቸው ዮናስም እንዲሁ በጸባዩ ምስጉን የሆነ የገዢው ፓርቲ ተቃዋሚ ነው። የፌደራል ፖሊሶች ወደ ወ/ሮ መንበረ ሆቴል ገብተው ሲጠጡ ከቆዩ በሁዋላ አንከፍልም በማለት መውጣታቸው ያበሳጨው ልጃቸው ወጣት ዮናስ ” የዚህ መንግስት አገልጋዮች ስለሆናችሁ ነው” በሚል ተናግሮአቸዋል። ወታደሮቹ ምንም ሳይሉ ወደ ካምፓቸው ካመሩ በሁዋላ ፣ ሌሊት ላይ መሳሪያቸውን ይዘው በመምጣት የዮናስ እናትን ቤት በር ሰብረው በመግባት ዮናስን በ5 ጥይት ደብድበውታል። እናቱ ወ/ሮ መንበረ ” እባካችሁ ልጄን አትገደሉብኝ” ሲሉዋቸው ፖሊሶቹ እርሳቸውንም በ5 ጥይቶች ገድለዋቸው ወደ ካምፓቸው ተመልሰዋል።

ድርጊቱ ያስቆጣቸው የከተማዋ ነዋሪዎች ከቀበር በፊት የተቃውሞ ሰልፍ ቢያደርጉም፣ በፖሊሶች ዱላ ተደብድበው ተበታትነዋል። ጅማ ጧት አካባቢ በተኩስ ስትናወጥ መዋሉዋንም ነዋሪዎች ተናግረዋል። በጉዳዩ ዙሪያ አንድ የጅማ ነዋሪ አነጋግረናል ከአንድ ሳምንት በፊት አንዋር የተባለ ወጣት በጩቤ በአሰቃቂ ሁኔታ ከተገደለ በሁዋላ ህዝብ ድርጊቱን ለመቃወም ወደ አደባባይ ቢወጣም በተመሳሳይ መልኩ በፖሊሶች ተደብድቦ ተባሯል።

ከአንድ ወር በፊት ደግሞ ኬኔዲ መንገሻ የሚባል አዲስ ቅጥር የመንግስት ሰራተኛ በፖሊሶች ተገድሏል። በአካባቢው የሰፈረው የፌደራል ፖሊስ በህዝቡ ላይ የሚወስደው እርምጃ መጨመሩ ህዝቡ በስጋት እንዲኖር አድርጎታል። ነዋሪዎች እንደሚሉት ሁኔታው ከአቅማቸው በላይ እየሆነ ነው።

የመረጃ  ምንጩ በጉዳዩ ዙሪያ ከከተማው ፖሊስ ለማጣራት ያደረገው ጥረት እንዳልተሳካ ተጠቁሟል፡፡

ምንጭ፡-ኢሳት ሬዲዮና ቴሌቪዥን

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: