ድምፃዊ ቴዲ አፍሮ ከሃገር እንዳይወጣ ታገደ

Teddy_Afroበአውሮፓና በተለያዩ መካከለኛው ምስራቅ ሀገራት በርካታ የሙዚቃ ኮንሰርቶቹን ለማቅረብ ወደ ባህር ማዶ ሊጓዝ የነበረው ታዋቂው ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ከሀገር እንዳይወጣ መታገዱ ተገለፀ። ቴዲ አፍሮ የሙዚቃ ኮንሰርቱን በፊንላንድ ሄልሲንኪ በነገው ዕለት ማቅረብ ይጀምራል ተብሎ ተጠብቆ ነበር፡፡ ለዚህም የሙዚቃ ባንዱ አባላትና ማናጀሩ ዘካርያስ ጌታቸው እዛው ፊላንድ ቢገቡም፤ ቴዲ ከሃገር እንዳይወጣ በደህንነቶች በመታገዱ ምክንያት የነገው የፊንላንድ ኮንሰርት መሰረዙን አዘጋጆቹ ከፊንላንድ ሄልሲንኪ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታው ቀዋል።

ከጥቂት ወራት በፊት ለቴዲ አፍሮ የበርካታ ወራት እስር በመንግስት በምክንያትነት የተገለፀችው ቢ ኤም ደብልዩ የቤት አውቶሞቢል ከገቢዎችና ጉሙሩክ ቀረጥ ጋር በተያያዘ ክፍያ ሳይፈፀም ወደ ሶስተኛ ወገን በሽያጭ አስተላልፏል በሚል ክስ ተመስርቶበት በዋስ ከተለቀቀ በኋላ ወደ አሜሪካ ሊሄድ ሲል እንዲሁ በደህነንቶች ተይዞ በቦሌ ኤርፖርት ሲጉላላ ከቆየ በኋላ የተለመደ የኮንሰርት ስራውን ቀጥሎ ወደ ሀገሩ መመለሱ አይዘነጋም፡፡ ይሁን እንጂ ህዳር 26 ቀን 2007 ዓ.ም. አርቲስቱ ከሀገር እንዳይወጣ ፓስፖርቱ በደህንነቶች ለጉዞ ዝግጅት ላይ እያለ ድንገት መነጠቁን እና ይህ እስከተዘገበበት ድረስም የጉዞ ሰነዱ እንዳልተመለሰለት መረጃዎች አመልክተዋል። ድምፃዊ ቴዲ አፍሮ ለምን ከሃገር እንዳይወጣ እንደታገደ እስካሁን የተገለፀ ነገር የለም:።

በሄል ሲንኪ ፊላንድ የቴዲ አፍሮን ኮንሰርት ለመታደም ትኬቱን የገዙ በርካታ ታዳሚዎች በጉጉት ይጠባበቁ የነበረ ሲሆን፤ከአቅም በላይ በተፈጠረ ችግር ኮንሰርቱን በዕለቱ ማቅረብ ስለማይቻል መሰረዙን አዘጋጁ ቲ-ፕሮሞሽን ከሄልሲንኪ ፊንላንድ አስታውቋል ። ይሁን እንጂ አዘጋጆች ኮንሰርቱ በመሰረዙ ምክንያት ትኬቱን የገዙ ሰዎች ገንዘባቸው ክፍያ በፈፀሙበት መንገድ እንደሚመለስላቸው እና በቅርቡም የታሰበው ኮንሰርት እንደሚካሄድ በመጠቆም፤ ችግሩ የተፈጠረው ከአርቲስቱና ከአዘጋጆቹ አቅም በላይ በሆነ ችግር በመሆኑ አዘጋጁ ይቅርታ ጠይቋል፡፡ ለኮንሰርቱ መሰረዝ የሆነው ችግር እንደተፈታም የሙዚቃ ድግሱ እንደሚቀጥል ተጠቁሟል፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: