9ኙ ፓርቲዎች ትብብር የጠሩት ሰላማዊ ሰልፍ በፖሊስ ድብደባና እስር ተቋረጠ

ዛሬ ህዳር 27 ቀን 2007 ዓ.ም. በ9ኙ ፓርቲዎች ለትብብር ለ24 ሰዓት በመስቀል አደባባይ የተጠራው የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ በደህንነት፣ ፌደራልና የአዲስ አበባ ፖሊስ ድብደባና እስር ምክንያት መቋረጡ ተገለፀ፡፡ ሰልፉን ሲያስተባብሩና ሲመሩ የነበሩ በርካታ የፓርቲዎቹ አባላትና ደጋፊዎች ተደብድበው መታሰራቸው የተጠቆመ ሲሆን፤ በተለይም ከአመራሮች የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት፣ የጌዴኦ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ሊቀመንበር አቶ አለሳ መንገሻ እና የከንባታ ህዝቦች ኮንግረንስ ሊቀመንበር አቶ ኤርጫፎ በፖሊስ ታግተው መታሰራቸውን መረጃዎች አመልክተዋል፡፡

vvvvvvከዋና አመራሮቹ በተጨማሪ አቶ ወሮታው ዋሴ፣ ብርሃኑ ተክለያሬድ፣ ኢየሩስ ተስፋው፣ ጋዜጠኛ በላይ ማናየ፣ ወይንሸት ሞላ፣ ሳሙኤል አበበ፣ እያስፔድ ተስፋዬ፣ሜሮን አለማየሁ፣ ንግስት ወንዲፍራው፣ ወይንሸት ንጉሴ፣ ምኞት መኮንን፣ አቤል ኤፍሬም፣ ኤፍሬም ደግፌ፣ ኃይለማሪያም፣ ሜሮን፣ ኢብራሂም አብዱልሰላም፣ እና ሌሎችም የትብብሩ አመራሮችና አባላት ከፍተኛ ቁጥር ባለው ፌደራል ፖሊስ መያዛቸውን እና በታገቱበት ድብደባ እየተፈፀመባቸው እንደነበር የነገረ ኢትዮጵያ ዘገባ አመልክቷል፡፡ ይህ እስከተዘገበበት ድረስ የታሰሩት አለመለቀቃቸውን ምንጮች ጠቁመዋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ በሰላማዊ ሰልፉ ወቅት የታፈሱት አመራሮች ቂርቆስ ፖፖላሬ ፖሊስ ጣቢያ እንደሚገኙ የተጠቆመ ሲሆን፤ ከታሰሩት መካከል ወጣት አቤል ኤፍሬም በተፈፀመበት ከፍተኛ ድብደባ ራሱን ስቶ የካቲት 12 ሆስፒታል እንተኛ እና አቶ ይልቃል ጌትነትም ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ቢቢ ኤን ሬዲዮን ጨምሮ የተለያዩ የማኀበራዊ ገፆች መረጃ አመልክቷል፡፡ ሰላማዊ ሰልፉን በተመለከተ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ፅህፈት ቤትና የካቢኔ ጉዳዮች ኃላፊ የሆኑት አቶ አሰግድ ጌታቸው ለከተማ አስተዳደሩ በከተማዋ ውስጥ የ24 ሰዓታት የአዳር ሰልፍ ለማካሄድ ጥያቄ ቀርቦ እንደነበርና አስተዳደሩ ግን ፍቃድ አለመስጠቱን መናገራቸውን ድሬ-ቲዩብ ዘግቧል፡፡

የመንግስት ሹሙ ለሰልፉ ፈቃድ አልሰጠንም ቢሉም፤ በህገ መንግስቱ አንቀፅ 30(1) ማንኛውም ሰው ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብቱ እንደሆነ እና ሰላማዊ ሰልፍን በተመለተ የወጣው አዋጅ እንደሚያመለክተው ከሆነ፤ የተቃውሞም ሆነ የድጋፍ ሰላማዊ ሰልፍ አደባባይ ለመውጣት ማሳወቅ እንጂ ማስፈቀድ ድንጋጌ እንደሌለ ይታወቃል፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: