የአንድነት ፓርቲ ልዩ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ሁለት አጀንዳዎችን አፀደቀ

udjትናንት አርብ ታህሳስ 3 ቀን 2007 ዓ.ም. አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ(አንድነት) በጠራው ልዩ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ሁለት አጀንዳዎችን በመወያየት ማፅደቁ ተሰማ፡፡ በመጀመሪያ አጀንዳነት የተነሳው የኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው በገዛ ፍቃዳቸው ከፓርቲው ፕሬዘዳንትነት ስልጣን መልቀቃቸውን ተከትሎ ብሔራዊ ምክር ቤቱ የሰየመውን ፕሬዝደንት ተወያይቶ ያፀደቀ ሲሆን፤ በሁለተኛ አጀንዳነት የተያዘው እና ምርጫ ቦርድ የጠቅላላ ጉባኤ አባላት ቁጥራችሁን አሳውቁኝ ባለው መሰረት የጠቅላላ ጉባኤ አባላት ቁጥርን ወስኗል፡፡

ጠቅላላ ጉባኤው ከሁለቱ አጀንዳዎች በተጨማሪ በተጓደሉ የኦዲትና ኢንስፔክሽን አባላት ምክንያት የማሟያ ምርጫንም ማድረጉ ታውቋል፡፡ የአንድነት ፓርቲ ጠቅላላ ጉባዔ አሁንም በተለያዩ የፓርቲውና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መምከሩን እንቀጠለ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ከውይይቱ በኋላም የተለያዩ ተጨማሪ አጀንዳዎችን ከማፅደቅ በተጨማሪ አንገብጋቢ በሆኑ ወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይም ውሳኔዎችን ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የፓርቲው ጠቅላላ ጉባዔ አባላትም ከአራቱም የሀገሪቱ አቅጣጫ ወደ አዲስ አበባ መምጣታቸው ተጠቁሟል፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: