የ6 የፖለቲካ ድርጅቶች ግንባር የሆነው የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሚክራሲያዊ አንድነት ግንባር (መድረክ)እሁድ ታህሣሥ 5 ቀን 2007 ዓ.ም. በአዲስ አበባ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ አደረገ፡፡ መድረክ ሰልፉን ያደረገው ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓትት ጀምሮ ሲሆን፤መነሻውን ከ4 ኪሎ ግንፍሌ ድልድይ አድርጎ በአዋሬ አልፎ መዳረሻውን በየካ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው የጥምቀተ ባህር ታቦት ማደሪያ አካባቢ በሚገኘው ኳስ ሜዳ ላይ መከናወኑ ተጠቁሟል፡፡
የግንባሩ መረጃዎች አንንደሚያመለክቱት በሰልፉ ላይ ከ8 ሺ በላይ የአዲስ ኣበባ ነዋሪዎች መሳተፋቸው ተጠቁሟል፡፡ በሰልፉ ላይ ከተጋበዙ ፓርቲዎች መካከል የአንድነት ፓርቲ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዘዳንት አቶ ተክሌ ና የፓርቲው አመራርና አባላትን ጨምሮ ሌሎች የፖለቲካ ፓርቲ አባላትም መሳተፋቸው ተጠቁሟል፡፡ የመድረኩ ሰላማዊ ሰልፍ በወጣቶች የመድረክ አመራር፣ የሴቶች ተወካይ፣ አቶ ቡልቻ ደመቅሳና የወቅቱ የመድረክ ሊቀ መንበር ፕሮፌሰር በየነ ዼጥሮስ ባሰሙት ንግግሮች መጠናቀቁን ምንጮች ከስፍራው አስታውቀዋል።
ሰላማዊ ሰልፉ የኢህኣዴግ መንግስት ሊያርማቸው የሚገቡ፣ መመቻቸት ያሉባቸው ፖለቲካዊ ምህዳር፣ መወገድ ያለበት የፀረ ሽብር ህግ ፣የ2007 ዓ.ም. ምርጫ ፍትሃዊ እንዲሆን ሊያደረጉ የሚገቡ ስራዎች እንዲሰሩ፣ በየቦታው እያጋጠመ ያለው አፈና፣ እስርና እንዲሁም ግድያዎች እንዲቆሙ በሰልፉ ላይ ከተሰሙ መፈክሮች በተጨማሪ የመድረኩ አመራሮች ጥሪ ማቅረባቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡