ኢትዮጵያዊውን የገደለው ቻይናዊ “ለሁለቱ አገራት መልካም ግንኙነት” ሲባል ክሱ እንዲቋረጥ ተደረገ

በምዕራብ ጎጃም ዞን ሰሜን አቸፈር ወረዳ ውስጥ ኢትዮጵያዊውን የገደለው ዠንግ ቢንዥንግ የተባለ ቻይናዊ ‹‹በቸልተኝነት ሰው በመግደል›› ወንጀል ክስ ተመስርቶበት የነበር ቢሆንም ‹‹ለሁለቱ አገራት መልካም ግንኙነት›› በሚል ትዕዛዝ ክሱ መቋረጡን ከክልሉ ፍትህ ቢሮ የተገኘው ሰነድ አጋለጠ፡፡

የአማራ ክልል ፍትሕ ቢሮ ለአቸፈር ወረዳ ፖሊስ ጽህፈት ቤት ተከሳሹ ካሳ ከፍሎ መውጣቱ ለሁለቱ አገራት መልካም ግንኙነት እንደሚበጅ በጻፈው ደብዳቤ ክሱ እንዲቋረጥ መደረጉን ‹‹በአማራ ፍትህ ቢሮ የምዕራብ ጎጃም ዞን የፍትሕ መምሪያ የወንጀል መዛግብት መርምሮ መወሰንና ተከራክሮ ማስወሰን የስራ ሂደት›› ለሰሜን አቸፈር ፖሊስ ጽህፈት ቤት በጻፈው ደብዳቤ ተመልክቷል፡፡ በትዕዛዙ መሰረትም ክሱ ቀሪ ሆኖ የምርመራ መዝገቡ ተመላሽ መደረጉን በደብዳቤው ላይ መገለፁን ነገረ-ኢትዮጵያ ዘግቧል፡፡

በ2004 ኣ.ም. በአርሲ በቻይና ኩባን ተቀጥረው የሚሰሩ ዘጎች በርካታ የሰብዓዊ መብት ጥሰት በቻይኖች ተፈፅሞባቸው አቤቱታ ቢያቀርቡ የኢትዮጵያ መንግስት ተበዳዮቹንና አቤቱታ አቅራቢዎቹን ለመግደልና ለማሰር በመሞከሩ የሰራተኛ ማኀበሩ አመራሮች ሀገር ጥለው መሰደዳቸው አይዘነጋም፡፡news pic

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: