የአንድነት ፓርቲ ሁለት አባላት ድብደባ ተፈፀመባቸው

ወይንሸት ስለሺ በህክምና ዕርዳታ ላይ

ወይንሸት ስለሺ በህክምና ዕርዳታ ላይ

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ (አንድነት) ፓርቲ የሴቶች ጉዳይ ምክትል ኃላፊ ወይንሸት  ስለሺ እና የፓርቲው አባል መሳይ ትኩ ባልታወቁ ሰዎች መደብደባቸው ተሰማ፡፡  ወጣት መሳይ ትኩ ባለፈው እሁድ ጥር 3 ቀን 2007 ዓ.ም. አንድነት ፓርቲ የጠራውን ጠቅላላ ጉባኤውን አጠናቆ ወደ ቤቱ ሲጓዝ አዲስ አበባ ራስ መኮንን ድልድይ አካባቢ ባልታወቁ ሰዎች ከፍተኛ ድብደባ እንደተፈፀመበት ፓርቲው አስታውቋል፡፡

በተመሳሳይ ዜና በፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የነበረችና በፓርቲው ንቁ ተሳትፎ እያደረገች የምትገኘው የሴቶች ጉዳይ ምክትል ኃላፊ ወይንሸት ስለሺ ጥር 6 ቀን 2007 ኣ.ም. ከረፋዱ 5፡30 ላይ አዲስ አበባ በተለምዶ ነፋስ ስልክ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ባልታወቁ ሁለት ሰዎች ከፍተኛ ድብደባ እንደደረሰባት የፍኖተ ነፃነት ዘገባ አመልክቷል፡፡ ወይንሸት ነፍሰጡር መሆኗንና ሆዷ ላይም ከፍተኛ ድብደባ በመፈፀሙ በአሁን ወቅት ራሷን ስታ ሆስፒታል የህክምና ዕርዳታ እየተደረገላት መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

መሳይ ትኩ

መሳይ ትኩ

ሁለቱም የፓርቲው አባላት በፓርቲው እንቅስቃሴ ላይ ንቁ ተሳትፎ እንደነበራቸው በመግለፅ፤ በተለይ ወጣት መሳይ ምርጫ ቦርድና ኢህአዴግ አንድነት መጪውን 2007 ኣ.ም. በሚደረገው ምርጫ እንዳይሳተፍ የሚደረገውን ሴራ ቀድሞ በማጋለጡ የተወሰደበት እርምጃ እንደሆነ የፍኖተ ነፃነት ዘገባ አመልክቷል፡፡ ወይንሸትም በፓርቲው ፕሬዘዳንታዊ ምርጫ አስመራጭ ኮሚቴ ሆና ከማገልገሏ በተጨማሪ በፓርቲው ላይ የሚደረጉ አፍራሽ እንቅስቃሴዎችን በማውገዝ አስተያየት መሰንዘሯ ለተፈፀመባት ድብደባ ምክንያት ሳይሆን እንዳልቀረ የፓርቲው ልሳን መረጃ አመልክቷል፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: