አዲስ አበባ በሚገኝ ትምህርት ቤት አጥር በመደርመሱ ከተጎዱት መካከል የአንዲት ተማሪ ህይወት አለፈ

በአደጋው ህይወቷ ያለፈው ተማሪ ፅዮን ንጉሴ

በአደጋው ህይወቷ ያለፈው ተማሪ ፅዮን ንጉሴ

ባለፈው ሳምንት በአዲስ አበባ ሳሪስ አካባቢ በሚገኘው ፍሬህይወት አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አጠገብ ከባቡር መንገድ ስራ ጋር በተያያዘ በተደረገ ቁፋሮ የትምህርት ቤቱ አጥር ተደርምሶ 11 ተማሪዎች ላይ ጉዳት አድርሶ የነበረ ሲሆን፤ ከተጎዱት መካከል ተማሪ ፅዮን ንጉሴ ሆስፒታል ውስጥ የህክምና ዕርዳታ እየተደረገላት በደረሰባት ከባድ ጉዳት ምክንያት ህይወቷ ማለፉ ተሰምቷል፡፡ የተማሪ ፅዮን ንጉሴ የቀብር ስነስርዓትም ዛሬ ሳሪስ አካባቢ በሚገኘው ብሔረ ፅጌ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን መፈፀሙን የደረሰን መረጃ አመልክቷል፡፡

የትምህርት ቤቱ አጥር የተደረመሰው ቻይናዎች ጥንቃቄ በጎደለው መልኩ አጥሩ ጥግ ቁፋሮ በሚያደርጉበት ወቅት ተማሪዎች ዕረፍት ላይ ስለነበሩ አንዳንዶቹ ሲጫወቱ ሌሎች ደግሞ በአጥሩ ጥቅ ሲያጠኑ አደጋው መድረሱን በወቅቱ የነበሩ የዓይን እማኞች ተናግራዋል፡፡ በወቅቱ በቻይናዎቹ ድርጊት የተበሳጩ ተማሪዎቹ ቁጣቸውን ሲገልፁ በስፍራው በነበሩ ቻይናዎችና የአዲስ አበባ ፖሊሶች በርካታ ተማሪዎች መደብደባቸውም ተጠቁሟል፡፡ ስለተፈጠረው አደጋም ሆነ ስለተማሪዎቹ ጉዳት የመንግስት አካላት እስካሁን ምንም ያሉት ነገር የለም፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: