ትናንት ምሽት በቡራዩ ከተማ በደረሰ ከባድ የመኪና አደጋ የ12 ሰዎች ሕይወት አለፈ

በቡራዩ ከተማ ልዩ ስሙ ቀርሳ በተባለው አካባቢ ትላንት የካቲት 9 ቀን 2007 ኣ.ም. ምሽት በደረሰ አሰቃቂ የመኪና አደጋ የ12 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ ሁለት ሰዎች ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል፡፡

አደጋው የደረሰው ትላንት ምሽት 1 ሰዓት ከ20 ደቂቃ ላይ ሲሆን፥ ወደ አዲስ አበባ ይመጣ የነበረ ሲኖ ትራክ የጭነት ተሽከርካሪ ከሚኒባስ ጋር በመጋጨቱ ነው።

በግጭቱ ሳቢያ የተነሳው ከባድ የእሳት አደጋም በመኪናው ውስጥ ለነበሩት ሰዎች ህይወት ማለፍ ምክንያት እንደሆነ ቢነገርም፤ የአደጋውን ምክንያት በተመለከተ ይህ እስከ ተዘገበበት ድረስ  ከገለልተኛ አካልም ሆነ ከፖሊስ ምርመራ የተገኘ ማረጋገጫ የለም፡፡

በአደጋው ወቅት በመኪናዎቹ ላይ የደረሰ ቃጠሎ

በአደጋው ወቅት በመኪናዎቹ ላይ የደረሰ ቃጠሎ

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: