ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ገንዘቤ ዲባባ በስዊድን ስቶኮሎም የ2015 ዓለም አቀፍ የ5,000 ሜትር የቤት ውስጥ ዓለም አቀፍ ውድድር አሸነፈች፡፡ አትሌት ገንዘቤ ውድድሩን ያሸነፈችው ከዚህ ቀደም ተመዝግቦ የነበረውን ክብረ-ወሰን በማሻሻል ነው፡፡
ገንዘቤ ውድድሩን ያሸነፈችው 14 ደቂቃ ከ18 ሰከንድ ከ86 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት ነው፡፡ በውድድሩ ከዚህ ቀደም የነበረው የዓለም ክብረወሰን 14 ደቂቃ ከ24 ሰከንድ ከ37 ማይክሮ ሰከንድ ሲሆን፤ ይህም በኢትዮጵያዊቷ አትሌት መሰረት ደፋር ተይዞ እንደነበር አይዘነጋም፡፡ አትሌት ገነዝቤ ዲባባ የአትሌት ጥሩነሽ እና የአትሌት እጅጋየሁ ዲባባ ታናሽ እህት ስትሆን፤ በተለይ ካለፉት ሁለት ዓመታት ወዲህ የተለያዩ ዓለም አቀፍ ውድድሮች ላይ አዳዲስ የዓለም ክብረወሰን እያስመዘገበች ማሸነፏ ይታወቃል፡፡