የኢሬቻ በዓል በደብረ ዝቋላ እንደሚከበር የተላለፈው ዘገባ ማስተባበያ እንዲሰጥበት ተወሰነ

    • ለአፈጻጸሙ የወረዳው እና የዞኑ አስተዳደር ባለሥልጣናት ሓላፊነት ወስደዋል
    • ከመጋቢት ክብረ በዓል በፊት ማስተባበያው እንዲተላለፍ ከስምምነት ተደርሷል
    • ከኹሉም አካላት የተውጣጣ የሽማግሌዎች ኮሚቴ የችግሩን ቆስቋሾች ያጣራል
    • በክብረ በዓሉ ቀን የተጠናከረ ጥበቃ እንዲደረግ መመሪያ ተሰጥቷል
    ዝቋላ አቡነ ገብረመንፈስቅዱስ ገዳም

    ዝቋላ አቡነ ገብረመንፈስቅዱስ ገዳም

    ደብረዘይት/ቢሾፍቱ አካባቢ በሚገኘውና ከ800 ዓመታት ዕድሜ በላይ ባስቆጠረውና በየዓመቱ መጋቢት 5 የሚከበረው ታሪካዊው ደብረ ከዋክብት ዝቋላ አቡነ ገብረመንፈስቅዱስ ገዳም የኢሬቻ በዓል ይከበራል በሚል በክልሉ ፕሬዘዳንት አቶ ሙክታር ከድር በተፃፈና በፀደቀ ደብዳቤ ማስታወቂያና ዜና ተላልፏል መባሉን ተከትሎ በአካባቢው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ኃይማኖት ተከታዮች፣ የሀገረ ስብከቱና የገዳሙ አስተዳዳሪ ለኦሮሚያ ክልል መስተዳደር፣ ለዞኑና ለወረዳው ለሚለከታቸው አካላት ቅሬታ አቅርበው ነበር፡፡ በዚህም መሰረት ፓትርያርኩ ብፁዕ አቡነ ማትያስ ቤተክርስቲያኗን በመወከል ጉዳዩ በህዝቡ መካከል ሆን ብሎ ግጭት ለመቀስቀስና አለመግባባት ለመፍጠር የተደረገ በመሆኑ ቤተክርስቲያኗ ድርጊቱን እንደምትቃወም የሚገልፅ ቅሬታ ለክልሉ መስተዳደር መላካቸው ታውቋል፡፡

    ማስታወቂያውና ዜናው እንዲተላለፍ የተደረገው በክልሉ አበገዳ ተወካዮች ስም ቢሆንም፤ አባገዳዎቹ እነሱ ይህንን ማስታወቂያም እንደማያውቁትና እንደማይመለከታቸው በመግለፅ በሁኔታው መገረማቸው ተጠቁሟል፡፡ ስለሆነም የኢሬቻ በዓል በደብረ ከዋክብት ዝቋላ ገዳም እንደሚከበር የተላለፈው ዘገባና ማስታወቂያ ማስተባበያ እንዲሰጥበት መወሰኑ ሰሞኑን ከክልሉ ባህልና ቱሪዝም የወጡ መረጃዎች አመልክተዋል፡፡ ይህንንም በተመለከተ ሐራ ዘተዋህዶ በአጭሩ የሚከተለውን አጠናቅሮታል፡፡

    • ለእኛ አዲስ ነገር ነው፤ እዚኽ ቦታ ኢሬቻ የለም፤ በአራት ወይም በስምንት ዓመት አንዴ ዝናም እምቢ እንዳይለን ገዳሙን አስፈቅደን ከምንፈጽመው ሥርዐት ውጭ በተነገረው መልኩ የሚከበር በዓል የለም፡፡ ያስተላለፉት መጠየቅ አለባቸው፡፡(የአባ ገዳ ተወካዮች)
    • ህብረተሰቡን ከእኛ ጋራ ሊያጣሉ የሚፈልጉ ግለሰብ አመራሮች አሉ፡፡ለተላለፈው መልእክት ሓላፊነት የሚወስድ አካል ካልተገኘ፣ የመጋቢት ክብረ በዓል ከመድረሱ በፊት በስሕተት የተላለፈ መኾኑ ይገለጽልን፡፡(የገዳሙ አስተዳደር)
    • እናንተ ሰላም ፍጠሩ፤ [በክብረ በዓሉ] ከተለመደው ውጭ አንዳችም የሚደረግ አይኖርም፤ ጥበቃውም እንዲጠናከር ይደረጋል፤የተላለፈውን ዘገባ አጣርተን በኦሮምኛ እና በአማርኛ ማስተባበያ እንዲሰጥበት እናደርጋለን፡፡(የዞን የአስተዳደርና ፀጥታ ኃላፊዎች)

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: