በአዲስ አበባ የተቃውሞና የሀዘን ሰልፍ በመንግሥት ተበተነ፤በሊቢያ አሁንም በርካታ ኢትዮጵያውን የአድኑን ጥሪ እያሰሙ ነው

ዛሬ ሚያዚያ 13 ቀን 2007 ዓ.ም. ባለፈው እሁድ በበኣለም አቀፉ አሸባሪው አይ ኤስ አይ ኤል በተባለው ቡድን በሊቢያ በጥቂቱ 28 ኢትዮጵያውያን በመገደላቸው በመላው ኢትዮጵያውያን ሀዘኑ የበረታ ቢሆንም፤ በአዲስ አበባ ግን ህዝቡ በራሱ አነሳሽነት የተቃውሞና የቁጣ ሰልፍ ወጥቶ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ህዝቡ ከተገደሉት መካከል የአዲስ አበባ ቂርቆስ ሰፈር ቀበሌ 25 ነዋሪ የነበሩት ጓደኛሞች ኢያሱ ይኮኖአምላክ እና ባልቻ በለጠ ቤተሰብ ልቅሶ ከደረሱ በኋላ በርካታ ሰዎች “አንመካም በጉልበታችን …” መዝሙር፣”ወያኔ ሌባ…ኢቴቪ ሌባ…መንግሥት የሌለው እዚህ ብቻ ነው፣ ታርዷል ወገኔ…” የሚሉ መፈክሮች፣ ልቅሶና ተቃውሞ እያሰሙ ወደ ቤተመንግሥት ለማቅናት ሲሞክሩ በተደጋጋሚ በአዲስ አበባና በፌደራል ፖሊስ ሲከለከሉ ታይቷል፡፡

ሚያዝያ 13 ቀን 2007 ዓ.ም. የነበረው ሰልፍ መስቀል አደባባይ አካባቢ

ሚያዝያ 13 ቀን 2007 ዓ.ም. የነበረው ሰልፍ መስቀል አደባባይ አካባቢ

ህዝቡ የመጀመሪያ መነሻውን ከልቅሶ ቤት ያደረገ ሲሆን በሌላ በኩል ከቄራ ቡልጋሪያ ሰፈርና ከሳሪስ ጎተራ ሪቼ መሷለኪያ ባለው መንገድ እንዲሁም ከሜክሲኮ መስመር ወደመስቀል አደባባይ ሲመጡ አብዛኞቹ በፖሊስ ድብደባና ክልከላ እንዲበተኑ መደረጉን ታውቋል፡፡ በመጨረሻም በተደጋጋሚ በፖሊስ አገታና የተደረገበት የሪቼው፤የሟቾቹ ቤተሰቦች ያሉበት ከቂርቆስ ሪቼ መስቀል አደባባይ የነበረው ሰልፍ እስጢፋኖስን አልፎ ወደ ውጭበ ጉዳይ ሚኒስቴር አካባቢ ሲደር ሙሉ ለሙሉ በፖሊስ ከታገተ ቧላ መንግሥት ለነገ ሐሙስ ሚያዚያ 14 ቀን 2007 ዓ.ም. ሰልፍ መጥራቱን አስታውቋል፡፡

protestdemonstartion 2

ዛሬ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም ድርጊቱን በማውገዝ ከነገ ጀምሮ የ3 ቀናት ብሔራዊ ሀዘን ያወጀ ሲሆን፤ የሀገሪቱ ሰንደቅዓላማም በመላ ሀገሪቱ እና የኢትዮጵያ ኤምባሲና ቆንስላ ጽህፈት ቤት በሚገኙበት ሁሉ ዝቅ ብሎ እንዲውለበለብ ተወስኗል፡፡ በተለይ በፓርላማ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም የተሰማቸውን ሀዘን ከገለፁ በኋላ መንግሥት እርምጃ እንደሚወስድ ቢናገሩም ምን ዓይነት እርምጃ በመንግሥት እንደሚወሰድ ግን እስካሁን በዝርዝር አልገለፁም፡፡

በኢትዮጵያውን ላይ በአሸባሪ ቡድኑ የተፈፀመውን ጥቃት ኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ፣ የአሜሪካ መንግሥት፣ በእንግሊዝ የኮፕቲክ ኦርቶዶክስ፣ የሮማ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን እና በውጭ የሚገኘው የኢትዮጵያው ፈርስት ሂጅራ ፋውንዴሽን በትናንትናው ዕለት ድርጊቱን ወዲያው አውግዘዋል፡፡ በሌላ በኩል የኢትዮጵ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት፣ መድረክ፣ ሰማያዊ ፓርቲ፣ ኢዴፓ፣ ድምፃችን ይሰማ ድርጊቱን በመቃወም አውግዘው መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

በ ISIL በሊቢያ ከተገደሉት መካከል ኢያሱ ይኮኖአምላክ እና ባልቻ በለጠ

በ ISIL በሊቢያ ከተገደሉት መካከል ኢያሱ ይኮኖአምላክ እና ባልቻ በለጠ

በተለይ ከህዝቡ ቁጣን የቀሰቀሰው የኢትዮጵ መንግሥት አሸባሪ ቡድኑ ኢትዮጵያውን ክርስቲያኖችን መግደሉን ቢያሳውቅም፤ የኢትዮጵያ መንግሥት እና በአዲስ አበባ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሲኖዶስ ድርጊቱ ቢያወግዙም ዜግነታቸው ኢትዮጵያውያን ስለመሆናቸው አላጣራንም ካሉ በሁለተኛው ቀን አምነው መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ መንግሥትም ሆነ ቤተክርስቲያኗ ከማመናቸው በፊት ከተገደሉት ኢትዮጵያውን መካከል የኢያሱ እና ባልቻ ቤተሰቦች ቀድመው በማወቅ ልቅሶ መቀመጣቸው ታውቋል፡፡ ይህም በህዝቡ ዘንድ ቅሬታን ፈጥሯል፡፡ ዛሬ ዘግይቶ በተገኘው መረጃ መሰረት ከተገደሉት መካከል ቀደም ሲል ኢያሱና ባልቻ የታወቁ ሲሆን፤አሁን ደግሞ ከመቀሌ አካባቢ የጅማ ዩኒቨረስቲ ምሩቅ የነበረው ዳንኤል ሓድሽ እና አለም ተስፋይ እንዲሁም አንድ ኤርትራዊ እንደነበሩበት መረጃዎች አመልክተዋል፡፡

የጂማ ዩኒቨርስቲ ምሩቅ የነበረውና በ ISIL የተገደለው ዳንኤል ሓዱሽ

የጂማ ዩኒቨርስቲ ምሩቅ የነበረውና በ ISIL የተገደለው ዳንኤል ሓዱሽ

የጂማ ዩኒቨርስቲ ምሩቅ የነበረውና በ ISIL የተገደለው ዳንኤል ሓዱሽ

የጂማ ዩኒቨርስቲ ምሩቅ የነበረውና በ ISIL የተገደለው ዳንኤል ሓዱሽ

በአሁን ሰዓትም በርካታ ኢትዮጵውያን ከሊቢያ ትሪፖሊ ባልታወቁ ሰዎች ታፍሰው መወሰዳቸውን እና በስከተማው እና በሊቢያ ባህር ዳርቻ አካባቢ ከአሸባሪ ቡድኑ ጥቃት የተደበቁ በርካታ ኢትዮጵያውያን የአድኑን ጥሪ በማሰማት ላይ ይገኛሉ፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: