ሰማያዊ ፓርቲ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች አባላቱ እየታሰሩና እየተደበደቡ መሆናቸው ገለፀ

በጋሞጎፋ ዞን በርካታ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች እየታደኑ እየታሰሩ መሆኑን የዞኑ የሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪዎች ገልጸዋል፡፡ ከትናንት ሚያዝያ 30 ቀን 2007 ዓ.ም ጀምሮ ጋሞ ጎፋ ዞን ጎፋ ወረዳ ሳውላ ከተማው ውስጥ በርካታ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች መታሰራቸውን የጋሞ ጎፋ ዞን ምንጮች አስታውቀዋል፡፡

Election

በተመሳሳይ በትናንትናው ዕለት በጋሞጎፋ ዞን ዳራማሎ ወረዳ ቅስቀሳ ላይ የነበሩ 17 የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ታስረዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በጋሞጎፋ ዞን ቦንኬ ወረዳ ለፖሊስ “ለሰማያዊ ፓርቲ የሚቀሰቅስ ማንኛውም አካል ላይ እርምጃ ውሰዱ” የሚል ትዕዛዝ መተላለፉን የዞኑ የሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪዎች ገልፀዋል፡፡

በሰሜን ወሎ ዞን ሀብሮ ወረዳ ጎራና ቀበሌ የሰማያዊ ፓርቲ የተወካዮች ምክር ቤት ዕጩ የሆነው አቶ ዮናታን ሰይድ በካድሬዎች ድብደባ እንደተፈፀመበት ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡ አቶ ዮናታን ዛሬ ከዋቱ 3፡20 አካባቢ ጊራና ከተማ ላይ የምርጫ ቅስቀሳ እያደረገ በነበረበት ወቅት የብአዴን/ኢህአዴግ ካድሬዎች ‹‹ለምን ትቀሰቅሷላችሁ? ደፍራችሁናል!›› በማለት ድብደባ እንደፈፀሙበት ገልጾአል፡፡ ሆስፒታል ሆኖ በስልክ ያነጋገረን አቶ ዮናታን በተለይ እግሩ ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰበት ገልጾአል፡፡

መንግስት ሚያዝያ 14 ቀን 2007 ዓ.ም አይ ኤስ አይ ኤስን ለማውገዝ በጠራው ሰልፍ ሰበብ እየታደኑ እየታሰሩ መሆኑን የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡ ሀሙስ ሚያዝያ 22 ቀን 2007 ዓ.ም ብሌን መስፍንና ተዋቸው ዳምጤ ከመስሪያ ቤት ተይዘው የታሰሩ ሲሆን ሚያዝያ 24 ቀን 2007 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀርበው ‹‹ሰላማዊ ሰልፉ ላይ የተደረገውን አመጽ መርታችኋል፡፡›› በሚል ፖሊስ ክስ እንዳቀረበባቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡

በተመሳሳይ ዛሬ ሚያዝያ 26 ቀን 2007 ዓ.ም ማቲያስ መኩሪያ ቤቱ ውስጥ እያለ በፖሊስ ተይዞ ታስሯል፡፡ ማቲያስ፣ ብሌንና ተዋቸው ወረዳ 10 (ላዛሪስት ፖሊስ ጣቢያ) ታስረው ይገኛሉ፡፡ ይህንን የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ የሚደረገው እስርም “መንግስት በሰማያዊ ፓርቲ ላይ የጀመረውን የሀሰት ክስ እውነት ለማስመሰል የታቀደ ነው፡፡ ፖሊስ ምርመራ ሳይጨርስ በሀሰት 20 አባላትንና 6 አመራሮችን አስረናል ብለው ነበር፡፡ እነሱ የፈለጉት ይህን ሚዲያ ላይ ወጥተው በሀሰት የፈፀሙትን ውንጀላ ማሰመሰል ነው፡፡” ሲል አቶ ዮናታን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡

በሌላ ዜና በየ ክፍለ ሀገሩ የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ ደህንነትና ፖሊስ የሚፈፅመው ድብደባ አሁንም መቀጠሉ ተገልጾአል፡፡ የደብረማርቆስ ከተማ ነዋሪና የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነችው የሀሳብ ጌታቸው “ለሰማያዊ ፓርቲ ወረቀት በትነሻል” በሚል ከፍተኛ ድብደባ እንደተፈፀሙባት ተገልጾአል፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: