የኢትዮጵያው አንጋፍው የትዝታ ሙዚቃ ንጉስ ድምፃዊ መሐሙድ አህመድ የሙዚቃ ህይወት የጀመረበት 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል ተከበረ፡፡ ነሐሴ 5 ቀን 2007 ዓ.ም. በሸራተን አዲስ ሆቴል በተካሄደ የእንኳን ደስ ያለህ መርሃ ግብር፤ አርቲስቱ በርካታ ሽልማቶችም ተበርክተውለታል፡፡ ድምፃዊው አሁን 75ኛ ዓመት ዕድሜ ባለፀጋ ቢሆንም፤ በመድረኩ እንደቀድሞ ሲያዜም ተስተውሏል፡
ድምፃዊ መሐሙድ አህመድ ቀደም ሲል የ2007 የቢቢሲ ዓለም አቀፍ የሙዚቃ ሽልማትን ጨምሮ በርካታ ሽልማቶችን ማግኘቱ ይታወቃል፡፡