የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን ድል ቀንቶታል

በጋቦን ለሚዘጋጀው የ2017ቱ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በምድብ 10 (J) ውስጥ የሚገኘውና በዮሐንስ ሳህሌ የሚሰለጥነው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን እሁድ ሰኔ 7 ቀን 2007 ዓ.ም. ከሌሶቶ አቻው ጋር በባህር ዳር ስታዲየም ባደረገው ጨዋታ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ በጫወታው የሌሶቶ ብሔራዊ ቡድን ቀድሞ ጎል ያስገባ ሲሆን፤ ለኢትዮጵያ አቻ የምታደርገውን ውጤት የኢትዮጵያ ቡና እግር ኳስ ክለብ ተጫዋች የሆነው ጋቶች ፓኖም አስቆጥሯል፡፡
በመጨረሻም ለግብፁ አል-ሃሊ ክለብ የሚጫወተው ሳላዲን ሰይድ ለኢትዮጵያ የማሸነፊያዋን ሁለተኛ ግብ በማስቆጠር በስታዲየሙ የነበረውን ታዳሚ እና በቴሌቪዥን መስኮት ጨወታውን ሲከታተል የነበረውን ህዝብ በደስታ አስፈንጥዟል፡፡ በጫወታውም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን 3 ነጥብና 1 ንፁህ ጎል ይዞ ወጥቷል፡፡ ከምድቡ አልጄሪያ ሲሼየልስን 4 ለ 0 በማሸነፍ በ3 ነጥብ እና በ4 ንፁህ ጎል ምድቡን እየመራች ስትገኝ፤ ኢትዮጵያ 3 ነጥብና 1 ንፁህ ጎል ይዛ ከምድቡ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ከሌሶቶ አቻው ጋር በባህርዳር ስታዲየም

የኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ከሌሶቶ አቻው ጋር በባህርዳር ስታዲየም

በቀጣይም የኢትዮጵያ ብሄራዊ እግር ኳስ ቡድን ነሐሴ 30 ቀን 2007 ዓ.ም. ሁለተኛ የምድብ ማጣሪያ ጫወታውን በሲሽየልስ ቪክቶሪያ ስታዲየም ከሲሽየልስ እግር ኳስ ቡድን አቻው ጋር ያደርጋል፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: