የታዋቂው ጠበቃ ተማም አባቡልጉ የጥብቅና ሙያቸው የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት የጥፋተኝነት ብይን በተላለፈበት ቀን መሰረዙ ታወቀ፡፡ ፍትህ ሚኒስቴር የአቶ ተማም አባቡልጉን ጥብቅና ለአንድ ዓመት ከሰባት ወር የጥብቅና ፈቃዳቸው መታገዱ ታውቋል፡፡
የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ፣ የፖለቲካ አመራሮች፣ ጋዜጠኞች እና በተለያዩ የህግ ጉዳዮች ጠበቃ የሆነው ጠበቃ ተማም አባቡልጉ በፍርድ ቤት ላይ በሚያደርጋቸው ክርክሮች በተለይም መንግስት ከጅሃዳዊ ሀረካት ጀምሮ የሰራቸውንና ኢትዮጵያ ውስጥ የፍትህ ስርዓቱን ዝቅጠት በመረጃና በህግ በማጣቀስ በተለያዩ ሚዲያዎች ላይ በማጋለጣቸው ምክንያት ከዚህ ክስ ተመስርቶባቸው እንደነበር ይታወቃ፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ማስፈራሪያና ዛቻዎች ከመፈጸማቸው ሌላ ድብደባ እንደተፈጸመባቸው ይታወቃል፡፡ ይህ እስከ ተዘገበበት ድረስ የፈቃዱ መሰረዝ ምክንያት አልታወቀም፡፡