ዛሬ ሰኞ ጳጉሜ 2 ቀን 2007 ዓ.ም. ለ36ተኛ ጊዜ፤ ለብይን ደግሞ ለ4ተኛ ጊዜ ተቀጥሮ የነበረው የዞን9 ብሎገሮች ጉዳይ በድጋሚ ለመስከረም 27 ቀን 2008 ዓ.ም. ተቀጠረ።
በሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ ለዛሬ በተደጋጋሚ የተላለፈው የብይን ፤ በድጋሚ ዳኞች አልተሟሉም በሚል ለ37ተኛ ጊዜ ተቀጥሯል።
በዳኞች አለመሟላት የተነሳ ችሎቱን ማስቻል አልችልም ብለው በቢሮ ተከሳሾችን እና ጠበቆችን የጠሩት ዳኛ ዘሪሁን ብይኑ ቢሰራም፤ ለማሳወቅ ሁሉም ዳኞች መገኘት ስላለባቸው ለመስከረም 27 ቀን 2008 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥተናል ብለዋል ።
ከአንድ ወር በኃላ በመደበኛው የፍርድ ቤት መከፈቻ የተቀጠረው ችሎት ተከሳሾች መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነፃ ይሰናበቱ ወይስ ይከላከሉ የሚለውን ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።
ምንጭ፡፤ ዞን 9 ማኀበራዊ ሚዲያ ገፅ