በየመን ሁቲ አማጽያን እጅ ለእስር ተዳርጎ የነበረው ጋዜጠኛ ግሩም ተክለኃይማኖት ከእስር ተፈትቶ ከቤተሰቡ ጋር ተቀላቅሏል። ጋዜጠኛ ግሩም ተክለኃይማኖት የታሰረበት ምክንያት ይደግፈው በነበረ አንድ ስደተኛ ኢትዮጵያዊ ጥቆማ ሲሆን ” በስደተኛው ስም እርዳታ ይሰበስባል ፣ ስለየመን የተለያዩ መረጃዎችም ወደ ውጭ ያቀብላል ” የሚል ክስ ተመስርቶበት ነበር ።
ጉዳዩን ያጣራው ፖሊስ በቀረበው ክስ ዙሪያ ጭብጥ መረጃ ማስረጃ በማጣቱ ግሩም በነጻ ተለቋል ። ከዚሁ ጋር በተያያዘ የከሳሽ ምስክር ሆነው የቀረቡት አብዛኛው ምስክሮች ” እውነትን በጥቅም አንለውጥም ” በሚል ከሳሽን በመክዳት ወደ ህሊናቸው መመላሳቸው ታውቋል ።