ባለፈው ጥቅምት 5 ቀን 2008 ዓ.ም. አራቱ የዞን ዘጠኝ አባላት መካከል ናትናኤል ፈለቀ፣ አቤል ዋበላ፣ አጥናፍ ብርሃኔ እና በሌለችበት ክስ የተመሰረተባት ሶሊያና ሽመልስ) በነፃ እንዲለቀቁ ሲወሰን፤ ዛሬ ጥቅምት 10 ቀን 2088 ዓ.ም. በዋለው ችሎት በወንጀለኛ መቅጫ ህግ 257/ሀ እንዲከላከል ተብይኖበት የነበረው በፍቃዱ ኃይሉ በ20 ሺህ ብር ዋስ ከእስር እንዲለቀቅ ተወሰነ፡፡
ብሎገርና ጋዜጠኛ በፍቃዱ ሀይሉ ጥቅምት 5 ቀን 2008 ዓ.ም ለልደታ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት የዋስትና መብቱ እንዲከበርለት ጠይቆ በነበረው መሰረት ለዛሬ ጥቅምት 10/2008 ዓ.ም የዋስትናውን ጉዳይ ለማየት ቀጠሮ የሰጠው የልደታ ፍርድ ቤት በ20 ሺህ ብር ዋስ ወጥቶ ጉዳዩን በውጭ ሆኖ እንዲከታተል ወስኗል፡፡
አራቱ የዞን ዘጠኝ አባላት መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነፃ እንዲሰናበቱ በተወሰነበት ወቅት ክሱ ከሽብርተኝነት ወጥቶ በማስረጃነት የቀረቡበት ፅሁፎች አመፅ ቀስቃሽ ናቸው በሚል በወንጀለኛ መቅጫ ህግ 257/ሀ እንዲከላከል የተወሰነበት በፍቃዱ ሀይሉ መከላከያ ምስክሮቹን እንዲያሰማ ለህዳር 27 ቀን 2008 ዓ.ም ቀጠሮ ተሰጥቶታል፡፡