አቃቤ ህግ በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ የሽብርተኝነት ክስ መስርቶባቸው በፌደራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነፃ እንዲሰናበቱ ተበይኖላቸው አቃቤ ህግ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ጠይቆባቸው ጉዳያቸውን በእስር ላይ ሆነው እየተከታተሉ የሚገኙት የተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮች በድጋሜ ለጥር 10 ቀን 2008 ዓ.ም ተቀጥረዋል፡፡
ዛሬ ታህሳስ 29 ቀን 2008 ዓ.ም ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በእነ ሀብታሙ አያሌው ላይ የተጠየቀው ይግባኝ ላይ ብይን ይሰጣል ተብሎ ቢጠበቅም ዳኛ ዳኜ መላኩ ‹‹የምንመረምረው ነገር አለ›› በሚል ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥተዋል፡፡
ይግባኝ የተጠየቀባቸው ተከሳሾች ሀብታሙ አያሌው፣ የሺዋስ አሰፋ፣ አብርሃ ደስታ፣ ዳንኤል ሺበሺ እና አብርሃም ሰለሞን ሲሆን፣ ሁሉም ተከሳሾች ነሀሴ 14 ቀን 2007 ዓ.ም በስር ፍርድ ቤት ነፃ ቢባሉም እስካሁን በእስር ላይ የሚገኙ ናቸው፡፡
ምንጭ፡ ነገረ ኢትዮጵያ