ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት የሆነው ሂውማን ራይትስ ዎች አራተኛ ወሩን ይዞ የቀጠለውን የኦሮሚያ ክልል ህዝባዊ ተቃውሞ ላይ መንግሥት በፀጥታ ኃይሉ በወሰደው የኃይል እርምጃ ሰዎች መደላቸውን፣ በርካታ ሰዎች መቁሰላቸውን እና መታሰራቸውን እንዲሁም ታግተው የደረሱበት ያልታወቁ ሰዎች መኖራቸውን በመግለፅ መግለጫ አወጣ፡፡
ሂውማን ራይትስ ዎች በመግለጫው “አጠቃላይ የተገደሉ ሰዎችን ቁጥር ለማረጋገጥ አልቻለም ምክንያቱም በኢትዮጵያ ያለው እንቅስቃሴ እና በነጻነት የመዘገብ ሁናቴ የተገደበ በመሆኑ ነው፡፡ ተሟጋቾች በተለይ ከማህበራዊ ድረ-ገፆችን መሰረት በማድረግ ባገኟቸው የቪዲዮ፣ የፎቶ እና የድረ-ገጽ ላይ ጽሁፎች መረጃዎች መሰረት ከኖቬምበር 12 ቀን ጀምሮ ከ200 በላይ ሰዎች መገደላቸውን ጠቁመዋል፡፡ ያለው መረጃ እንሚጠቁመው በበርካታ ሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ታስረዋል፤ በርካቶቹ የት እንሚገኙም አይታወቀም፤ የሚገመተው በሃይል እንዲሰወሩ መደረጉን አስታውቋል፡፡
እ.አ.አ.ከህዳር ወር 2015 ዓ.ም. ጀምሮ በኦሮሚያ ክልል በስፋት እየተካሄደ ያለውን ሰላማዊ ተቃውሞ የኢትዮጵያ የጸጥታ ሃይል በጉልበት እያፈነው እንደሚገኝ ሂውማን ራይትስ ዎች አስታወቀ፡፡ ከ2016 ዓ.ም. መነሻ ጀምሮ በእየለቱ ሰዎች እንደሚገደሉ እና በዘፈቀደ እንደሚታሰሩ በመግፅ፤ የወታደራዊ ሰራዊትን ያካተተው የጸጥታ ሃይል ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ ላይ የሚገኙ በርካታ ሰዎችን ቀጥታ በመተኮስ ገድሏል፡፡ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ታስረው ያለምንም ክስ እንደታገቱ ይገኛሉ፡፡ ባለፉት ሳምንታት የተቃውሞው ድግግሞሽ የቀነሰ መስሎ ቢታይም አፈናው ግን ቀጥሏል፡፡” ይላል ፤በመግለጫው፡፡
የተቋሙን ሙሉ መግለጫ (በአማርኛ እና በእንግሊዘኛ) ለማግኘት የሚከተለውን ሊንክ ይጠቀሙ፤
ምንጭ፡ https://www.hrw.org/am/news/2016/02/21/287126
https://www.hrw.org/news/2016/02/22/ethiopia-no-let-crackdown-protests