በደቡብ ክልል ሱርማ በሚገኙ የሙርሲ ማኀበረሰብ ላይ የመንግሥት ልዩ ኃይል የወሰደው እርምጃና ያለተገባ አያያዝ በርካታ ኢትዮጵያውያንን አስቆጣ!

ቀኑ በትክክል ባይታወቅም ባለፈው ሳምንት የተከናወነ እንደሆነ የሚታመነውና በፖሊስ ቁጥጥር ስር ባልተገባ አያያዝ እርቃናቸውን ይታዩ የነበሩ በደቡብ ክልል በቤንች ማጂ ዞን የሚገኙ እና የደቡብ ኦሞ ዞን አጎራባች የሆኑት የሙርሲ ማኀበረሰብ በአካባቢው በመንግሥት ለማከናወን የታቀደውን የኩራዝ ስኳር ፕሮጀክት ማስፋፊያ ባደረሰባቸው ተፅዕኖ ተቃውሞ ማሰማታቸውን ተከትሎ የተሰጠ የመንግሥት ምላሽ መሆኑ እየተነገረ ነው፡፡

human-right-abuse-ethiopia4

በተለይ በክልሉ ልዩ ኃይል ፖሊስ ቁጥጥር ስር የነበሩት የሙርሲ ማኀበረሰብ አባላት ኢሰብዓዊ በሆነና ለህይወታቸው በሚያሰጋ መልኩ እር በርስ በመጠላለፍ የታሰሩበት ሁኔታ ቁጣን ቀስቅሷል፡፡ ይንንም በተመለከተ የስርዓቱ ደጋፊዎች ምስሉ ኢትዮጵያ ውስጥ የተፈፀመ ሳይሆን ደቡብ ሱዳን በሚል ለማስተባበል ከመሞከራቸው በስተቀር ከመንግሥት በኩል የተሰጠ ምላሽ የለም፡፡

Mursi HR violation

መረጃዎች እንደሚያሳዩት በቁጥጥር ስር የነበሩት የሙርሲ ማኀበረሰብ እርቃናቸውን እር በርስ በአሰቃቂ ሁኔታ ካሰሯቸው መካከል የሁለቱ ፖሊስ አባላት ማንነት ከነ ምስላቸው በሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪ ኢትዮጵያውን መለየት መቻላቸው ተጠቁሟል፡፡

ከታሰሩት ጋር ይታዩ ከነበሩት ፖሊሶች መካከል ሁለቱ ማንነታቸው የተለየ ሲሆን፤ እነሱም ኮንስታብል ደመቀ አራርሳ ወጊ የሚባል የወለንጪቲ ተወላጅ ሲሆን፤ ረዳት ኮንስታብል የኑስ ተማም ቦሬ የሚባል የዲላ ተወላጅ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡ በቁጥጥር ስር የነበሩ አካላትን ጭኖ የነበረው ተሽከርካሪ ንብረትነቱ እና ፖሊሶቹ ለብሰውት የነበረው የደንብ ልብስ የደቡብ ክልል ልዩ የፖሊስ ኃይል እንደነበርም መረጃዎች አመልክተዋል፡፡

ይሁን እንጂ፤ የፖሊስን ኢ-ሰብዓዊ አያያዝ በተመለከተ የረህ እስከተዘገበበት ድረስ ከኢትዮጵያ መንግሥት የተሰጠ ማስተባበያም ሆነ ማረጋገጫ የለም፡፡

በአካባቢው ከዚህ በፊት መንግሥት ያለምንም በቂ ማኀበራዊና አካባቢዊ ተፅዕኖ ግምገማ እናያለ በቂ ካሳ ከ200 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ማፈናቀሉ ከፍተኛ ትችት አስከትሎ እንደነበር ይታወሳል፡፡

 

 

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: