ሜዲትራኒያን ባህር ላይ በሰጠመችው ጀልባ አደጋ ምክንያት ከሞቱት መካከል ኢትዮጵያውያንም ይገኙበታል

(አዲስ ሚዲያ) ትናንት እሁድ ሚያዝያ 9 ቀን 2008 ዓ.ም. ጠዋት 400 ያህል ስደተኞችን ጭና ከግብፅ ወደ ጣሊያን ስታመራ የነበረች ጀልባ ሜዴትራንያን ባህር ላይ በመስጠሟ በርካታ ሰዎች መሞታቸው ተገለፀ ፡፡

Meditreanian sea Boat sinks

በጀልባዋ ሲጓዙ የነበሩት አብዛኛው ኢትዮጵያውያንና ሶማሊያውያን ሲሆኑ የተወሰኑ ኤርትራውያን ስደተኞች እንደሚገኙበት እየተነገረ ሲሆን፤ የሶማሊያ መንግሥት በበኩሉ 200 ያህል ዜጎቹ በአደጋው መሞታቸውን አስታውቋል፡፡ ከሞቱት መካከል ኢትዮጵያውያን እናት እና ልጅን ጨምሮ በርካታ ወጣቶችም በአደጋው ህይወታቸው እንዳለፈ መረጃዎች አመልክተዋል፡፡ በጀልባው ላይ ሲጓዙ ከነበሩት መካከል ከ200 ያላነሱት ኢትዮጵያውያን እንደነበሩም ተጠቁሟል፡፡

በተለይ በጉዞ ላይ እያሉ የአደጋው ሰለባ የሆኑት ከህዳር አጋማሽ 2008 ዓ.ም. በኦሮሚያ እየተደረገ ባለው ህዝባዊ ተቃውሞ መንግሥት እየወሰደ ያለውን ወታደራዊ የኃይል እርምጃ በመፍራት አብዛኛው ከባሌ፣ከሐረር እና ድሬዳዋ አካባቢ የተሰደዱ ኢትዮጵያውን እንደሆኑ ቤተሰቦቻቸውን ዋቢ በማድረግ የኢሳት ዘግቧል፡፡

የጀልባዋን መስጠም ተከትሎ በአቅራቢያ የደረሱት ዓለም አቀፍ የነፍስ አድን ሰራተኞች ከ27 ያላነሱ የአደጋው ሰለባ ሰዎችን ህይወት ማትረፍ መቻላቸው የተገለፀ ሲሆን፤ ከሞቱት መካከልም የተወሰኑ አስከሬኖችን አውጥተዋል፡፡ ይሁን እንጂ እስካሁን በአጠቃላይ ምን ያህል ሰዎች እንደሞቱ እና ምን ያህሉ እንደተረፉ የተሰጠ ዝርዝር መረጃ የለም፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: