በአርባምንጭ አካባቢ የመንግሥት ወታደሮች ላይ ጥቃት ተፈፀመ

(አዲስ ሚዲያ) በአርባ ምንጭ ነጭ ሳር አካባቢ ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች የመንሥት ወታደሮች ላይ ድንገተኛ ጥቃት አደረሱ፡፡ በጥቃቱ የአካባቢው ወታደራዊ አዛዥን ጨምሮ ከ20 ያላነሱ የመንግሥት ወታደሮች መገደላቸውን እና ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ በርካታ ወታደሮችም ጉዳት ደርሶባቸው በአርባምንጭና በአካባቢው ባሉ የጤና ተቋማት የህክምና ዕርዳት እየተደረገላቸው መሆኑን ከስፍራው የዓይን እማኞችን ጠቅሶ ኢሳት ዘግቧል፡፡ የተፈፀመውን ጥቃት በተመለከተ መንግሥት በመግለጫው እንዳተተው ከሆነ፤ ጥቃቱ የፈፀሙ አካላት ከኤርትራ ስልጠና ወስደው በዩጋንዳ፣ ኬንያ፣ ሞያሌ አድርገው ወደ አርባምንጭ አከባቢ እንደመጡ፤ ጥቃት አድራሾችም በፀጥታ ኃይሉ እንደተማረኩ አስታውቋል፡፡

Arbegnoch ginbot 7 force

መንግሥት ጥቃት አድራሾቹ እነማን እንደነበሩ እና ቁጥራቸው ምን ያህል እንደሆነ ከመግለፅ ተቆጥቧል፡፡
ይሁን እንጂ በስሩ ባሉ መገናና ብዙኃን እና በመንግሥት ኮሚኒኬሽን ጽህፈት ቤት ገፅ ላይ ጥቃት አድራሾቹ ከነትጥቃቸው እንደተማረኩ በማስመሰል በአንድ ወቅት አሜሪካ በኢራቅ ከታጣቂዎች ማረኩት ብላ ያሰራጨው ምስል በማኀበራዊ ሚዲያ ከተጋለጠ በኋላ መንግሥት ማረኩት ያለውን የተሳሳተ መረጃ ምስልን ከአንድ ቀን በኋላ ከገፁ ላይ አንስቶታል፡፡

ማክሰኞ ግንቦት 2 ቀን 2008 ዓ.ም. በዚህ በአርባ ምንጭ አካባቢ በመንግሥት ኃይሎች ላይ ለተፈፀመው ጥቃት ስርዓቱን በሁለገብ ትግል ለመጣል በይፋ የሚንቀሳቀሰው አርቦኞች ግንቦት 7 ለአንደነት እና ለዴሞክራሲ ንቅናቄ (አርበኞች ግንቦት 7) ኃላፊነቱን ወስዷል፡፡ በተለይ የድርጅቱ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ለአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ እና ለኢሳት በሰጡት ቃለመጠይቅ ላይ አርበኞች ግንቦት 7 በመንግሥት ወታደሮች ላይ በአርባምንጭ አካባቢ ጥቃት መፈፀሙን አረጋግጠዋል፡፡
እንደ ፕሮፌሰሩ ገለፃ ከሆነ ድርጅቱ ሀገር ውስጥ ከሚንቀሳቀሰው እና በደቡብ ካለው አነስተኛ ቡድን የተሰነዘር ጥቃት መሆኑን እና የጦር መሳሪያውንም ቢሆን ያገኙት ከራሱ ከመንግሥት ኃይሎች መሆኑን በማረጋገጥ በሌሎች የአሀገሪቱ አካባቢዎችም ተመሳሳይ ጥቃት በመንግሥት ላይ እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል፡፡

ፕሮፌሰሩ አክለውም አርበኞች ግንቦት 7 የሚታገለው ኤርትራ ውስጥ ሳይሆን ሀገር ቤት ኢትዮጵያ ውስጥ መሆኑን እና በሁሉም የሀገሪቱ አቅጣጫ እየተንቀሳቀሰ ስለመሆኑ የአርባምንጩ ጥቂት ማሳያ እንደሆነ በመግለፅ የስርዓት ለውጥ እስካልመጣ ድረስ ወደፊትም ተመሳሳይ ጥቃቶች በመንግሥት ላይ የሚቀጥሉ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡ በጥቃቱም ከአርበኞች ግንቦት 7 በኩል በመንግሥት ወታደሮች በተወሰደ የፀፋ ርምጃ ምን ያህል ጉዳት እንደደረሰ ከመግለፅ ተቆጥበዋል፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: