የሶማሊያው እስላማዊ ታጣቂ አል-ሸባብ 43 የኢትዮጵያ ወታደሮች መግደሉን አስታወቀ

(አዲስ ሚዲያ) አል-ሸባብ ጥቃቱን የፈፀመው ከዋና ከተማዋ ሞቃዲሾ በስተሰሜን 300 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ሃልገን ከተማ፤ የአፍሪካ ህብረት ሰላም አስከባሪ ልዑክ( አሚሶም) አባል በሆኑ የኢትዮጵያ ወታደሮች ላይ መሆኑን ሮይተርስ እና አል-ጀዚራን ጨምሮ የተለያዩ ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል፡፡

Ethiopian troops in Somalia

በተለይ የታጣቂ ቡድኑ ወታደራዊ ክንፍ ቃል አቀባይ ሺክ አብዱዓሲስ አቡ ሙሳብ ለሮይተርስ እንደገለፁት ከሆነ፤ ትናንት ሐሙስ ሰኔ 2 ቀን 2008 ዓ.ም. በማዕከላዊ ሶማሊያ ሂራን ክልል ከተማ በሆነችው ሃልገን በፈፀሙት ጥቃት 43 የኢትዮጵያ ወታደሮችን መግደላቸውን፣ ቁጥሩን በይፋ ባይገልፁም በነበረው ውጊያ ከራሳቸው ከታጣቂ ቡድኑም የተገደሉ እንዳሉ አረጋግጠዋል፡፡

የኢትዮጵያ መንግሥት በበኩሉ በቃል አቀባዩ በኩል በኢቢሲ በኩል ባስተላለፈው መግለጫ 245 የአልሸ-ሸባብ ታጣቂዎችን መግደሉን ቢያስታውቅም፤ በውጊያው ምን ያህል የኢትዮጵያ ወታደር እንደተገደለ የገለፀው ነገር የለም፡፡

የኢትዮጵያ ጦር በኢህአዴግ ውሳኔ ወደ ሶማሊያ ከገባ ጀምሮ በርካታ ወታደሮች እንደተገደሉና ጉዳት እንደደረሰባቸው በተወሰነ ደረጃ ታጣቁ ቡድኑ በተለያየ ጊዜ ካሰራጨው የተገደሉ ኢትዮጵያውያን ወታደሮች ስም እና ማንነት በስተቀር፤እስካሁን በኢትዮጵያ ወታደሮች ላይ ስለደረሰ ጉዳት በመንግሥት በኩል ለህዝብ የተሰጠ መግለጫም ሆነ ማብራሪያ የለም፡፡ ይሁን እንጂ ለተመሳሳይ ተልዕኮ በአፍሪካ ህብረት አሚሶም የተሰማሩ የኬንያ፣ ዩጋንዳ፣ ጅቡቲ ወታደሮች ከአል-ሸባብ ጋር በተደረጉ ውጊያዎች የደረሱ ጉዳቶችንም ሆነ ድሎች በተለያየ ጊዜ ለህዝባቸው ሲገልፁ ተስተውሏል፡፡

የኢህአዴግ መራሹ መንግሥት በይፋ ወታደሮቹን ወደ ሶማሊያ ካዘመተ ከ7 ዓመታት በላይ ቢሆንም፤ እስካሁን በኢትዮጵያ ወታደሮች ላይ ስለደረሰው ጉዳት በመንግሥት በኩል ይፋ ተደርጎ ባያውቅም፤ የስርዓቱ ደጋፊ ብሎገሮች በትናንትናው የአል-ሸባብ ጥቃት 9 ያህል የኢትዮጵያ ወታደሮች ሞታቸውን እና 248 የታጣቂው ቡድንም በኢትዮጵያ ወታደሮች እንደተገደሉ ገልፀዋል፡፡

በሐሙሱ የአል-ሸባብ ጥቃት በሶማሊያ ውስጥ ስለተገደሉ የኢትዮጵያ ወታደሮች የኢትዮጵያ መንግሥት ምን የገለፀው ነገር ባይኖርም፤ ጥቃቱን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ ባን ኪ ሙን በይፋ አውግዘዋል፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: