የኢትዮጵያ መንግሥት በአሜሪካን ሀገር የፈፀመውን ህግወጥ የቦንድ ሽያጭ ገንዘብ ከነወለዱ እንዲመልስ ተወሰነበት

(አዲስ ሚዲያ) የኢትዮጵያ መንግስት በአሜሪካን ህገወጥ የቦንድ ሽያጭ በማድረግ የሰበሰበውን ገንዘብ እንዲመልስ ተወሰነበት። የአሜሪካን የቦንድ ሽያጭና ግዥን የሚቆጣጠረው ኮሚሽን ባቀረበው ክስ መሰረት፤ የኢትዮጵያ መንግስት መብራት ኃይል ኮርፖሬሽን በአሜሪካን ባልተመዘገበ የቦንድ ሽያጭ የሰበሰበውን 5.8ሚሊዮን ዶላር እና 6 መቶ ሺህ ዶላር ወለድን ጨምሮ በድምሩ 6.45 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር እንዲከፍል ተስማምቷል።

sec-logo

የኢትዮጵያ መንግሥት ከ2004 ዓ.ም. እስከ 2006 ዓ.ም. በህገወጥ መንገድ ገንዘቡን ሰብስቦት የነበረው ነዋሪነታቸው በአሜሪካን ሀገር ከሆኑ 3,100 ኢትዮጵያውያን ነበር፡፡ ስለሆነም በቦንድ ግዥ የተሰበሰበው ገንዘብ በሙሉ ከነ ወለዱ እንዲመለስ የተደረገው፤ የአሜሪካን ሴኩዩሪቲ ኤንድ ኤክስቼንጅ ኮሚሽን (SEC) ህግን ተላልፎ በመገኘቱ መሆኑን የኮሚሽኑ መግለጫ አስታውቋል። የኢትዮጵያ መንግሥትም የአሜሪካን ህግ በመጣስ የቦንድ ሽያጭ ማካሄዱን በማመን፤ የቦንድ ሙሉ ሽያጩን ከነ ወለዱ ለአሜሪካ መንግሥት ለሚመለከተው አካል ለመክፈል መስማማቱን ኮሚሽኑ በዋሸንግተን ዲሲ ሰኔ 1 ቀን 2008 ዓ.ም. በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል፡፡

ምንጭ፡- http://www.sec.gov/news/pressrelease/2016-113.html

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: