በኢትዮጵያ የጥራት ጉድለት የተገኘባቸው 69 ሚሊየን ኮንዶሞች ተገኙ

በያዝነው 2008 ዓ.ም. ሁለተኛ አጋማሽ የጥራት ጉድለት የተገኘባቸው 69 ሚሊየን ኮንዶሞች ሊወገዱ ነው።
ከግሎባል ፈንድ በተገኘ ከ2 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር የተገዙት ኮንዶሞች፥ በኢትዮጵያ የምግብ መድሃኒትና ጤና አጠባበቅ ቁጥጥር ባለስልጣን ፍተሻ የጥራት ችግር እንዳለባቸው ተጋግጧል።

Condoms

ኮንዶሞቹ ከሁለት ወራት በፊት በተደረገ ፍተሻ መያዛቸው ነው የተገለጸው። የመድሃኒት ፈንድና አቅርቦት ኤጀንሲ ዋና ዳይተሬክር አቶ መስቀሌ እንደተናገሩት፥ የኮንዶሞቹ አቅራቢ ድርጅት ለግዢ የወጣውን ገንዘብ እንዲተካ የማድረግ ስራ እየተሰራ ይገኛል።
ኮንዶሞች ለገበያ ከመቅረባቸው በፊት ጥብቅ የጥራት ፍተሻ እንደሚደረግላቸው ያነሱት ዳይሬክተሩ፥ ይህ ስራም ጥራቱ ተረጋግጦ ገበያ ላይ ከዋለ በኋላ በአያያዝ ምክንያት ሊደርስ የሚችል ችግርንም እስከ መፈተሽ ድረስ የሚከናወን ነው ብለዋል ሲል ፋናቢሲ ዘግቧል፡፡
ጥራት የጎደላቸው 69 ሚሊዮን ኮንደሞች በአንድ የህንድ ኩባንያ አማካኝነት በኢትዮጵያ መሰራጨታቸውን በተመለከተ ቀደም ሲል ዋዜማ ሬዲዮ መዘገቡ ይታወሳል፡፡

የተሰራጩት ኮንዶሞች ጫፋቸው የተቀደዱ፣ ፈሳሽ እና አየር ማሳለፍ የሚችሉ፣በላዩ ላይ ያለው ማለስለሻ ቅባት ከሰውነት ፈሳሽ ጋር ሲደባለቅ የጤና ችግር የሚፈጥር እንደሆነ በተደረገ ምርመራ መረጋገጡ ተጠቁሟል፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: