(አዲስ ሚዲያ) የበርካታ ዓለም አቀፍ የሩጫ ውድድር ክብረ ወሰን ባለቤት የሆነው አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዘዳንት ሆኖ ተመረጠ፡፡ ምርጫው የተደረገው ጥቅምት 25 ቀን 2009 ዓ.ም. አትሌቲክስ ፌዴሬሽኑ በጠራው ጠቅላላ ጉባኤ ሲሆን፤ በውድድሩም አቶ ተፈራ ሞላ እና አቶ ዳኛቸው ሽፈራው ተሳታፊዎች ነበሩ፡፡ በመጨረሻም የአዲስ አበባ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንን በመወከል የተወዳደረው አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ከነበሩት አምስት ድምፆች መካከል የዘጠኙን በማገኘት በማሸነፉ ለሚቀጥሉት አራት ዓመታት ፌዴሬሽኑን እንዲመራ በፕሬዘዳንት ተመርጧል፡፡
አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ( ፎቶ ክሬዲት ቢቢሲ)
ከአትሌት ሻለቃ ኃይሌ በተጨማሪ ለስራ አስፈፃሚነት አትሌት ኮሎኔል ደራርቱ ቱሉ፣ አትሌት ገዛኸኝ አበራ፣ አትሌት ገብረእግዚአብሔር ገብረማርያም በእጩነት ቀርበው ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ለስራ አስፈፃሚነት አሸናፊ ሆኖ የተመረጠው አትሌት ገብረእግዚአብሔር ገብረማርያም መሆኑ ታውቋል፡፡
ቀደም ሲል ለሀገሪቱ የአትሌቲክ ውጤት መውረድ ከፌዴሬሽኑ በተጨማሪ በጋራ ሲሰራ የነበረው የኢትዮጵያ አትሌቶች ማኀበር አመራር የነበሩት አትሌት መሰረት ደፋር እና አትሌት ስለሺ ስህን በተለይ ከአትሌቶች ተመሳሳይ ቅሬታ ሲቀርብባቸው የነበረ ቢሆንም፤ በአዲስ ስራ አስፈፃሚ ውስጥ በድጋሚ አባል እንዲሆኑ መደረጉም ተጠቁሟል፡፡
በተለይ ባለፈው በለንደን ኦሎምፒክ እና በቀርቡ በተካሄደው የሪዮ ዲ ጄኔሪዮ ኦሎምፒክ የአትዮጵያ አትልቲክስ ዓለም አቀፍ የኦሎምፒክ ውድድር ባልተለመደ መልኩ እየቀነሰ በመሄዱና ብት ያላቸው ተወዳዳሪዎች ለውድድር ለምን አልተጋበዙም በሚል የስፖርቱ ደጋፊና አፍቃሪ እንዲሁም አትሌት ኃይሌ እና አትሌት ገብረእግዚአብሔርን ጨምሮ በርካታ ዓለም አቀፍ ስመ ጥር አትሌቶች በይፋ ቅሬታ ማሰማታቸው ይታወሳል፡፡
የአትሌት ኃይሌ ለፕሬዘዳንት መመረጥና የአትሌት ገብረእግዚአብሐየር ለስራ አስፈፃሚነት መመረጥ ከስፖርቲ ደጋፊና አፍቃሪ ኢተዮጵያውያን በተጨማሪ ከዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ማኀበርም የእንኳን ደስ ያላችሁ ድጋፍ ተችሯቸዋል፡፡