ዶ/ር መረራ ጉዲና ያቀረቡት የዋስትና መብት ጥያቄ ውድቅ ተደረገባቸው

(አዲስ ሚዲያ) ባለፈው የካቲት 24 ቀን 2009 ዓ. ም. በነበረው ቀጠሮ ዶ/ር መረራ ጉዲና በጠበቃቸው አማካኝነት የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ጥያቄ አቅርበው ነበር። በዚህም ምክንያት የካቲት 30 ቀን 2009 ዓ. ም. አቃቤ ህግ ባቀረበው የዋስትና ጥያቄ ላይ ያለውን ተቃውሞ አቅርቦ፤ ለመጋቢት 1 ቀን 2009 ዓ. ም. ተይዞ የነበረው ቀጠሮ በዋስትናው ጉዳይ ላይ መርምሮ ብይን ለመስጠት ነበር።

Dr.Merera Gudina

ዶ/ር መረራ ጉዲና

ዳኞች በሁለቱም ወገን የቀረበውን ክርክር መመርመራቸውን ገልፀዋል፥ የዋስትና መብት በህገ መንግስቱ የተደነገገ ቢሆንም ፍፁም መብት ሳይሆን በህግ አግባብ ሊገደብ የሚችል እንደሆነ ጠቅሰው ዶ/ር መረራ ያቀረቡትን የዋስትና ጥያቄ ከዚህ አግባብ መታየት ያለበት ጉዳይ እንደሆነ ተናግረዋል።

ዳኞች በማስከተልም የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ስነ-ስርዐት አንቀፅ 63 ንዑስ አንቀፅ 1 ላይ “ማንኛውም የተያዘ ሰው የተከሰሰበት ወንጀል የሞት ቅጣትን ወይም አስራ አምስት አመት ወይም በላይ የሆነ ፅኑ እስራት የማያስቀጣ ከሆነ እና ወንጀል የተፈፀመበት ሰው በደረሰበት ጉዳት የማይሞት የሆነ እንደ ሆነ ፍርድ ቤቱ የዋስትና ወረቀት አስፈርሞ መልቀቅ ይችላል፡፡” እንደሚል ጠቅሰው፤ ዶ/ር መረራ ላይ የቀረበባቸው የመጀመሪያ ክስ (ወንጀለኛ መቅጫ አንቀፅ 32፣ 38 እና 238) የሚያስቀጣው የእድሜ ልክ እስራት ወይም የሞት ቅጣት በመሆኑ የዋስትና መብት እንደማይፈቀድላቸው ገልፀው ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ሆነው ክሳቸውን እንዲከታተሉ አዘዋል።

ዶ/ር መረራም የዋስትና መብት እንዳልተፈቀደላቸው ከሰሙ በኋላ

“1ኛ.ከእነ ጄኔራል መንግስቱ ንዋይና ጄኔራል ታደሰ ብሩ ዘመን ጀምሮ ከአንድ ትውልድ በላይ ገዳዮችን፣ ሟቾች፣ አሳሪዎችና ታሳሪዎች በበዙበት የሃገራችን የፓለቲካ አላማ ውስጥ በመቆየት አንድ ከሆዱ በላይ ለሃገሩ የሚያስብ ምሁር ማድረግ እንዳለበት ሁሉ ከአርባ አምስት ዓመታት በላይ ለሃገሬ የተሻለ ለውጥ እንዲመጣ መታገሌ እየታወቀ ወደ ጎን መገፋቱ ፤
2ኛ. ለሁላችንም የምትሆንና በእኩልነት የምታስተናግደን፣ ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ እንድትፈጠር ነፃ የፍትህ ስርአት በሃገራችን እንዲሰፍን ላለፉት 25 አመታት በመታገሌ፤ መከሰሴ አንሶ የሃገሪቱ ፓርላማ አባል ጭምር የነበርኩ ሰው ለተራ ወንጀለኛ የሚፈቅድ የዋስ መብት በመከልከሌ የተሰማኝ ጥልቅ ሃዘን ለራሴ ብቻ ሳይሆን እኛም ሆነ ልጆቻችን በሰላም ይኖሩበታል ለምንለው መከረኛ ሃገራችን አላልፍለት ብሎ ሲታመስ ለሚኖረው መከረኛ ህዝባችን ጭምር መሆኑን እንዲታወቅልኝ ነው።” ሲሉ ተናግረዋል።

በመጨረሻም በክሱ ላይ የሚቀርብ መቃወሚያ ለመቀበል ለሚያዚያ 16 ቀን 2009 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል። የተቀሩት ተከሳሾችን በተመለከተ በጋዜጣ እንዲወጣ የታዘዘው የጥሪ ማስታወቂያን ለማየት ለመጋቢት 29 ቀን 2009 ዓ. ም. የተያዘው ቀጠሮ እንደተጠበቀ መሆኑን በመግለፅ በዕለቱም ዶ/ር መረራ መቅረብ እንዳለባቸው ፍርድ ቤቱ ሲናገር ተደምጧል።

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: