የቀድሞው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ስነ ምድራዊ ጤና መምህር የነበሩት አቶ ፈቃደ ሽዋቀና ባጋጠማቸው የጤና ችግር ምክንያት በህክምና ሲረዱ ቆይተው ግንቦት 1 ቀን 2009 ዓ.ም. በስደት ይኖሩ ከነበረበት አሜሪካ ህይወታቸው አልፏል።
አቶ ፈቃደ ሸዋቀና ህወሓት/ኢህአዴግ ግንቦት 1983 ዓ ም አዲስ አበባ ገብቶ ስልጣን ከተቆጣጠረ በኋላ ወዲያ 42 የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህራን በሟቹ ጠቅላይ ሚንስትር አቶ መለስ ዜና ትዕዛዝ ከተባአረሩ አንዱ ነበሩ።
አቶ ሸዋቀና ከስራቸው እንዲባአረሩ ከተደረጉ ብሏላ ወደ አሜሪካ በመሰደድ በሙያቸው የአንድ SCG ኩባንያ የስነምድር ጤና ተንታኝ በመሆን ለ25 ዓመታት አገልግለዋል። ከሙያቸው በተጨማሪ በይበልጥ በተለያዩ ፅንፍና ጠርዝ ላይ ያለውን የኢትዮጵያ ፖለቲካ ወደ መሐል ለማምጣት ባደረጉት የአስታራቂነት ሚና እና ጥረት በሁሉም የፖለቲካ ኃይሎች እምነትና ከበሬታን ማግኘት የቻሉ እንደነበሩ ይነገርላቸዋል።
የቀብር ስነ ስርዓታቸውም በስደት ዓለም በቆዩባት አሜሪካ እንደሚፈፀም የደረሰን መረጃ አመልክቷል።