የሰማያዊ ፓርቲ አመራር የነበረውና የመብት አራማጅ ዮናታን ተስፋዬ 6 ዓመት ከ6 ወር እስራት ተፈረደበት

(አዲስ ሚዲያ) የሰማያዊ ፓርቲ የቀድሞ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ፥ የ2007 ዓ. ም. በአዲስ አበባ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዕጩና የመብት አራማጅ ወጣት ዮናታን ተስፋዬ ግንቦት 17 ቀን 2009 ዓ ም በዋለው ችሎት 6 ዓመት ከ6 ወር እስር ተፈርዶበታል።

yonatan-tesfaye

ዮናታን ተስፋዬ

ወጣት ዮናታን ከህዳር 2008 ዓ. ም. ጀምሮ የተነሳውን ህዝባዊ አመፅ ተከትሎ ከታሰሩት በርካታ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና የመብት ተሟጋቾች መካከል አንዱ ነው።

ወጣት ዮናታን ተስፋዬ ደም ልገሳን ጭምሮ በተለያዩ ግብረ ሰናይ ተግባራት ላይም ይሳተፍ የነበረ ቢሆንም፥ ከታህሳሥ 17 ቀን 2008 ዓ ም ጀምሮ በእስር ላይ ይገኛል።

የፌደራል አቃቤ ህግ ክስ የመሰረተበት በፌስ ቡክ ማኅበራዊ ገፅ መንግሥት በዜጎች ላይ እየወሰደ የነበረውን ርምጃ የሚቃወሙና የሚተቹ ፅሑፎችን ፅፏል በሚል እንደሆነ የተመሰረተበት የክስ ሰነድ ያመለክታል።

በመጨረሻም የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የአዲስ አበባ ልደታ ምድብ ችሎት ግንቦት 17 ቀን 2009 ዓ ም በዋለው ችሎት በፌስ ቡክ ማኅበራዊ ገፅ የፃፋቸውን ፅሑፎች ብቻ እንደመረጃና ማስረጃ በመጠቀም 6 ዓመት ከ6 ወር እስራት ፈርዶበታል።

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: