የቀድሞው አንድነት ፓርቲ አመራር የነበረችው አስቴር ስዩም ተፈረደባት

(አዲስ ሚዲያ) ወጣት አስቴር ስዩም የታአሰረችው ከሰኔ 25 ቀን 2007 ዓ ም ጀምሮ ትኖርበት ከነበረው ጎንደር ከእስር በተጨማሪ በርካታ ዜጎች በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች መገደላቸውን መቃወም ተከትሎ በደህንነት ኃይሎች ታፍነው አዲስ አበባ ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ለወራት ከፍተኛ ስቃይና እንግልት ከደረሰባችው ሴቶችና ወጣቶች መካከል አንዷ ናት።

Aster Seyoum

አስቴር ስዩም

የቀረበባትም ክስ ህዝባዊ አመፅ ማነሳሳት ሙከራ በሚል  የፌደራል አቃቤ ህግ ክስ እንደነበር ያገኘው መረጃ አመልክቷል።

አስቴር ታፍና በመወሰድ ስትታሰር የ3 ወር ህፃን ልጇን ለወላጅ እናቷ ትታ የነበረ ቢሆንም፥ በማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ታስራ እያለ ወላጅ እናቷ ህይወታቸው ማለፉ ታውቋል።

ይሁን እንጂ፤ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት፥ የአድስ አበባ ልደታ ምድብ ችሎች ከ 23 ወራት እስርና የፍርድ ሂደት በኋላ ግንቦት 14 ቀን 2009 ዓ ም የ 4 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶባታል።

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: