ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው አንድ ዓመት ከ6 ወር እስር ተፈረደበት

(አዲስ ሚዲያ) የነገረ ኢትዮጵያ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው በፌደራል አቃብ ህግ በተመሰረተበት ክስ ከአንድ ዓመት ከ አምስት ወር እስር በኋላ የፌደራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት አዲስ አበባ ልደታ ምድብ ችሎት ግንቦት 18 ቀን 2009 ዓ. ም. የ 1 ዓምት ከ 6 ወር የቅጣት እስር ፈርዶበታል።

Getachew Shiferaw

ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው

ጋዜጠኛው ከህዳር 2008 ዓ. ም. ጅምሮ የነበረውን ህዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ ሲታሰር፥ ቀደም ሲል የሽብርተኝነት ክስ ተመስርቶበት የነበረ ቢሆንም፤ በመጨረሻም ፍርድ ቤቱ ክሱን ወደ መደበኛ ወንጀል ክስ ዝቅ በማድረግ አመፅ ማነሳሳት በሚል ክስ የቅጣት ውሳኔውን ማሳለፉን አሳውቋል። ይሁን እንጂ ጋዜጠኛው ለተላለፈበት የቅጣት ውሳን ብይን የቅጣት ማቅለያ እንዲያቀርብ ፍርድ ቤቱ ቢጠይቀውም ጋዜጠናው ባልሰራሁት ወንጀል የምጠይቀው የቅጣት ማቅለያ የለም በማለት የፍርድ ቤቱን ጥያቄ ውድቅ ማድረጉ ታውቋል።

ጋዜጠኛው ክስ የተመሰረተበትና የ1 ዓመት ከ6 ወር እስር ቅጣት የተጣለበት፤ በፌስ ቡክ ማኅበራው ሚዲያ በውጭ ከሚገኝ ጋዜጠኛ በተለይም መቀመጫውን ዋሸንግተን ዲሲ ካደረገው ጋዜጠኛ አበበ ገላው ጋር መልዕክት ተለዋውጠሃል፥ አመፅ ቀስቅሰሃል የሚል እንደነበር የቀረበበት ክስ አመልክቷል።

ጋዜጠኛው ህትመቱና ስርጭቱ በመንግሥት እንዲቋረጥ ከተደረገው የነገረ ኢትዮጵያ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ሆኖ ከማገልገሉ በተጨማሪ በተለያዩ መፅሔቶች፥ ጋዜጦችና ድረ-ገፆች ላይም የተለያዩ ፖለቲካዊ፥ ሰብዓዊ መብትና ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደረጉ በርካታ ፅሑፎችንም ያበረክት እንደነበር ይታወቃል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ሰኔ 2006 ዓ ም በመንግሥት እውቅና ተነፍጎት አባላቱና አመራሩ ምንም ዓይነት የስራ እንቅስቃሴ እንዳያደርጉ እግድ የተጣለብት የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ (ኢጋመ) መስራችና አስተባባሪ እንደነበር ይታወቃል።

ጋዜጠኛ ጌታቸው ከታህሳሥ 15 ቀን 2008 ዓ ም ጀምሮ በእስር ላይ ይገኛል።

በተለይ መንግሥት ህዝባዊ አመፁን ተከትሎ በወሰደው ርምጃ ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራውን ጨምሮ፥ ሌሎች ጋዜጠኞችና 60 ሺህ ያህል ሰላማዊ ዜጎች መታሰራቸውን የሀገርው ውስጥ የሰብዓዊ መብት አራማጆችና ተሟጋቾች መረጃ አመልክቷል።

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: