ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ የተፈረደበትን ፅኑ እስራት ጊዜውን አጠናቆ ወጣ

የቀድሞው ፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ የነበረው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ተፈርዶበት የነበረውን የ3 ዓመት ፅኑ እስራት አጠናቆ በጣ። ጋዜጠኛው የእስር ጊዜውን ካጠናቀቀ ሁለት ቀናት ቢያልፉትም፤ ዛሬ ጥቅምት 5 ቀን 2010 ዓ.ም. መለቀቁ ታውቋል።

journalist-temesgen-desalegn

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ    ፎቶ_ ከማኅበራዊ ገፅ
ጋዜጠኛው ከመታሰሩ በፊት በባለቤትነት እና በዋና አዘጋጅነት ከሚያስተዳድረው ፍትህ ጋዜጣ በተጨማሪ፥ በልዕልና ጋዜጣ፥ በአዲስ ታየምስ እና በፋክት መፅሔቶች ላይም በቋሚነት ይፅፍ እንደነበር ይታወቃል።

ጋዜጠኛ ተመስገን ለእስር የተዳረገውም ቀደም ሲል በፍትህ ጋዜጣ በፃፋቸው ፅሑፎች እንደነበር ቀርቦበት የነበረው የክስ ሰነድ ያስረዳል።

በኢትዮጵያ ምንም እንኳ ጋዜጠኛ ተመስገን የተፈረደበትን የእስር ጊዜ አጠናቆ ቢወጣም ፤ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬን ጨምሮ ሌሎች ጋዜጠኞች እና ብሎገሮች አሁንም ድረስ በእስር ላይ እንደሚገኙ ይታወቃል።

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: