የቀድሞው ፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ የነበረው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ተፈርዶበት የነበረውን የ3 ዓመት ፅኑ እስራት አጠናቆ በጣ። ጋዜጠኛው የእስር ጊዜውን ካጠናቀቀ ሁለት ቀናት ቢያልፉትም፤ ዛሬ ጥቅምት 5 ቀን 2010 ዓ.ም. መለቀቁ ታውቋል።
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ፎቶ_ ከማኅበራዊ ገፅ
ጋዜጠኛው ከመታሰሩ በፊት በባለቤትነት እና በዋና አዘጋጅነት ከሚያስተዳድረው ፍትህ ጋዜጣ በተጨማሪ፥ በልዕልና ጋዜጣ፥ በአዲስ ታየምስ እና በፋክት መፅሔቶች ላይም በቋሚነት ይፅፍ እንደነበር ይታወቃል።
ጋዜጠኛ ተመስገን ለእስር የተዳረገውም ቀደም ሲል በፍትህ ጋዜጣ በፃፋቸው ፅሑፎች እንደነበር ቀርቦበት የነበረው የክስ ሰነድ ያስረዳል።
በኢትዮጵያ ምንም እንኳ ጋዜጠኛ ተመስገን የተፈረደበትን የእስር ጊዜ አጠናቆ ቢወጣም ፤ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬን ጨምሮ ሌሎች ጋዜጠኞች እና ብሎገሮች አሁንም ድረስ በእስር ላይ እንደሚገኙ ይታወቃል።