የአርበኞች ግንቦት 7 አባል ናችሁ ተብለው ክስ የተመሰረተባቸው በአርባምንጭ ከተማ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ፍርድ ቤት ቀረቡ

የአርበኞች ግንቦት 7 አባል ናችሁ ተብለው ክስ የተመሰረተባቸው በአርባምንጭ ከተማ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት እነ ሉሉ መሰለ ዛሬ ጥቅምት 9፣ 2010 ከፍተኛ ፍርድ ቤት 4ኛ ችሎት ቀርበው ነበር።
★በመዝገቡ ክስ የተመሰረተባቸው 13 ሰዎች ሲሆኑ በብይን አንዱ ነፃ ሲወጣ (መሃመድ ዳና) 12ቱ እንዲከላከሉ ተበይኖ ነበር።

★ እንዲከላከሉ ከተባሉት ውስጥ 5ቱ (አለም ክንፈ፣ በረከት ተገኔ፣ ደረጄ አደመ፣ ሲሳይ አምባው እና አጥናፉ አበራ) አንከላከልም በማለታቸው መጋቢት 29 ቀን 2009 አራት አመት ከአምስት ወር ተፈርዶባቸዋል።

★እንከላከላለን ያሉት የተቀሩት ሰባቱ (ሉሉ መሰለ፣ አየለች አበበ፣ በጋሻው ዱንጋ፣ ዘኪዎስ ዘሪሁን፣ ጌታሁን ቃፃ፣ መርዶኪዮስ ሽብሩ እና ያረጋል ሙሉአለም) በግንቦት ወር 2009 ውስጥ መከላከያ ምስክሮቻቸውን አሰምተው አጨርሰዋል።

★በባለፈው አመት በተደጋጋሚ ለፍርድ ተቀጥረው የነበረ ቢሆንም የምስክሮች ቃል አልተገለበጠም እየተባለ ተለዋጭ ቀጠሮ ሲሰጣቸው የነበረ ሲሆን የዛሬውም ቀጠሮ ፍርዱን ለማሳወቅ ነበር።

★ሆኖም ዳኞች ፍርዱን ሰርተው እንዳልጨረሱ በመግለፅ “ለጥቅምት 28 ለማድረስ እንሞክራለን” ብለዋል።
★ በተደጋጋሚ በሚሰጠው ቀጠሮ የተማረሩት ተከሳሾቹን በመወከል 1ኛ ተከሳሽ ሉሉ መሰለ ይህን ብለዋል። “2008 የተከፈተ መዝገብ ነው። ባለፈው አመት ግንቦት ላይ ነው መከለከያ ምስክር አሰምተን የጨረስነው። ከኛ በኋላ መከላከያ ምስክር ያሰሙ ፍርድ ተሰርቶላቸዋል። የኛ በምን ምክንያት እንደዘገየ አላቅም። ቤተሰቦቻችን ከ500 ኪሜ ርቀት ነው ሚጠይቁን። እየተንገላቱ ነው። ጠያቂም የለንም።”
★እነ ሉሉ መሰለ በጥቅምት ወር 2008 በፖሊስ ተይዘው ማእከላዊ 4ት ወር ቆይተው የካቲት ወር 2008 ላይ ነው ክስ የተመሰረተባቸው።

ምንጭ፦ የፍርድ ቤት ውሎዎች

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: